ፍጹም ሙሉ እና በሙሉ የተመሰረተ፤ በሙሉ ጻድቅ። ፍጹም ደግሞም ኃጢያት ወይም ክፋት የሌለው ማለት ሊሆን ይችላል። ክርስቶስ ብቻ ነው በሙሉ ፍጹም የነበረው። የክርስቶስ እውነተኛ ተከታዮች በእርሱ ጸጋ እና የኃጢያት ክፍያ በኩል ፍጹም መሆን ይችላሉ። ከአምላካችን ከእግዚአብሔር ጋር ልባችሁ ፍጹም ይሁን, ፩ ነገሥ. ፰፥፷፩. እንግዲህ የሰማዩ አባታችሁ ፍጹም እንደ ሆነ እናንተም ፍጹማን ሁኑ, ማቴ. ፭፥፵፰ (፫ ኔፊ ፲፪፥፵፰). በቃል የማይሰናከል ማንም ቢኖር እርሱ ፍጹም ሰው ነው, ያዕ. ፫፥፪. እምነት ስለ ነገሮች ፍፁም የሆነ እውቀት አለ ማለት አይደለም, አልማ ፴፪፥፳፩፣ ፳፮. እግዚአብሔርም ፍፁም አምላክ ይሆን ዘንድ፣ የኃጢያት ክፍያ ተከፈለ, አልማ ፵፪፥፲፭. ሞሮኒ ፍፁም የሆነ ዕውቀት ያለው ሰው ነበር, አልማ ፵፰፥፲፩–፲፫፣ ፲፯–፲፰. አንድ ነገር ከእግዚአብሔር ወይም ከዲያብሎስ ለማወቅ እያንዳንዱ ሰው እንዲፈርዱ እና ፍፁም በሆነ ዕውቀትእንዲያውቁ የክርስቶስ መንፈስ ተሰጥቷቸዋል, ሞሮኒ ፯፥፲፭–፲፯. ወደ ክርስቶስ ኑ፣ እናም በእርሱም ፍፁማን ሁኑ, ሞሮኒ ፲፥፴፪. ፍጹም እስክትሆኑ ድረስ በትግስት ቀጥሉ, ት. እና ቃ. ፷፯፥፲፫. እነዚህ ፍጹም የሆኑት ጻድቅ ሰዎች ናቸው, ት. እና ቃ. ፸፮፥፷፱. የቤተክርስቲያኗ ሀላፊነቶች የተሰጡት ለቅዱሳን ፍጹምነት ነው, ት. እና ቃ. ፻፳፬፥፻፵፫ (ኤፌ. ፬፥፲፩–፲፫). ያለሙታናችን ፍጹም ልንሆን አንችልም, ት. እና ቃ. ፻፳፰፥፲፭፣ ፲፰. ኖኅ በዘመኑ ከነበሩት ሰዎች ሁሉ ይልቅ ጻድቅና ከበደል የራቀ ሰው ነበር, ሙሴ ፰፥፳፯.