የጥናት እርዳታዎች
መፅሐፍ ቅዱስ


መፅሐፍ ቅዱስ

መለኮታዊ ራዕያትን የያዙ የእብራውያን እና የክርስቲያን ፅሑፎች የተሰበሰበበት። በእንግሊዝኛ ቋንቋ ባይብል ማለር “መፅሐፍት” ማለት ነው። መፅሐፍ ቅዱስ በመንፈስ ቅዱስ ተፅዕኖ የተሰሩ የብዙ ነቢያት እና የተነሳሱ ጻፊዎች ስራ ነው (፪ ጴጥ. ፩፥፳፩)።

የክርስትያን መፅሐፍ ቅዱስ እንደ ብሉይ እና አዲስ ኪዳን የሚታወቁ ሁለት ክፍሎች አሉት። ብሉይ ኪዳን በጌታ በፍልስጥኤም አይሁዶች መካከል በስጋዊ አገልግሎቱ ጉዞ የሚጠቀሙባቸው ቅዱስ መጻሕፍትን የሚያካትት ነው። አዲስ ኪዳን በሐዋሪያት ዘመን የነበሩትን ፅሑፎች የያዘ እና እንደ አይሁዳዊ ቅዱሣት መጻህፍት አንድ አይነት ቅድስና እና ስልጣን እንዳለው የሚመለከት ነው። የብሉይ ኪዳን መጻሕፍት ከብዙ መቶ አመቶች የተዘረጋ ከዜጋዊ ፅሁፎችን የተወሰዱ እና በሙሉ በእብራውያን ቋንቋ የተጻፉ ነበሩ፣ ይህም ሲሆን የአዲስ ኪዳን መጻሕፍት የአንድ ትውልድ ስራዎች ናቸው እና በአብዛኛው የተጻፉት በግሪክ ቋንቋ ነበር።

በብሉይ ኪዳን ውስጥ ኪዳን የሚባለው ቃል “ቃል ኪዳን” የሚለውን የእብራዊያን ቋንቋ ቃል ያመለክታል። የድሮው ቃል ኪዳንም እስራኤል የእግዚአብሔር ህዝብ ከስጋዊ ህይወት ጀምሮ የነበራቸውን የወንጌሉን ሙሉነት ባስወገዱበት ጊዜ ለሙሴ የተሰጠው ህግ ነው። አዲሱ ቃል ኪዳን ኢየሱስ ክርስቶስ ያስተማረው ወንጌል ነው።

በእብራውያን መፅሐፍ ቅዱስ (ብሉይ ኪዳን) መፅሐፎቹ በሶስት ክፍሎች የተከፋፈሉ ናቸው፥ ህግ፣ ነቢያት፣ እና ፅህፈቶች። ክርስቲያናት የሚጠቀሙበት መፅሐፍ ቅዱስ መፅሀፎችን እንደ ታሪካዊ፣ ግጥም፣ እና ትንቢታዊ በሚለው ርእስ መሰረት ይከፋፍሏቸዋል።

የአዲስ ኪዳን መጻህፍት በብዙ ጊዜ በዚህ መሰረት ናቸው፥ አራቱ ወንጌሎች እና የሐዋርያት ስራዎች፤ የጳውሎስ መልእክቶች፤ የያዕቆብ፣ የጴጥሮስ፣ የዮሐንስ፣ እና የይሁድ አጠቃላይ መልእክቶች፤ እና የዮሐንስ ራዕይ።

የኋለኛው ቀን ቅዱሳን የኢየሱስ ክርስቶስ ቤተክርስትያን አባላት ቅዱሣት መጻህፍትን ያወድሳሉና ያከብራሉ እናም በመጨረሻው ቀናት እግዚአብሔር ከሰው ልጅ ጋር ያለውን የግንኙነት ታሪክን ለማረጋገጥና ለመደገፍ ተጨማሪ ራዕዮችን ጌታ በመስጠት እንደሚቀጥል ያረጋግጣሉ።