የጥናት እርዳታዎች
መግቢያ


የቅዱሳት መጻህፍት መመሪያ

የቅዱሳት መጻህፍት መመሪያ በመፅሐፍ ቅዱስ፣ በመፅሐፈ ሞርሞን፣ በትምህርት እና ቃል ኪዳኖች፣ እና በታላቅ ዋጋ ዕንቁ ውስጥ የሚገኙትን የተመረጡ ትምህርቶችን፣ መሰረታዊ መመሪያዎችን፣ ሰዎች፣ እና ቦታዎችን የሚያብራራ ነው። ይህም ለእያንዳንዱ ርዕስ ጥናታችሁ ዋና የቅዱሳት መጻህፍት ማጣቀሻ ያቀርብላችኋል። ይህ መመሪያ በግል እና በቤተሰባችሁ የቅዱሳት መጻህፍት ጥናት ሊረዳችሁ ይችላል። ስለወንጌል ያላችሁን ጥያቄ ለመመለስ፣ ለቅዱሳት መጻህፍት ርዕሶች ጥናት፣ ንግግሮች እና ትምህርቶችን ለማዘጋጀት፣ እና ስለወንጌል ያላችሁን እውቀት እና ምስክር ለማሳደግ ይረዳችኋል።

የሚቀጥለው ስዕላዊ መግለጫ በቅዱሳት መጻህፍት መመሪያ ውስጥ የሚገኘው ጥቅሰት ምሳሌን ይገልጻል።

ምስል
ምሳሌ

ምድር

በእግዚአብሔር በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል ሰው በስጋዊ ሙከራ ጊዜው እንዲጠቀሙበት የተፈጠረ የምንኖርበት ፕላኔት። የመጨረሻ እጣ ፈንታዋ የምትከበርና ከፍ የተደረገች መሆን ነው (ት. እና ቃ. ፸፯፥፩–፪፤ ፻፴፥፰–፱)። ምድር ለሰለስቲያል ክብር ብቁ ሆነው ለኖሩት ዘለአለማዊ ውርስ ትሆናለች(ት. እና ቃ. ፹፰፥፲፬–፳፮)። እነርሱም በአብና ወልድ ፊት በመኖር ይደሰታሉ (ት. እና ቃ. ፸፮፥፷፪)።

ለሰው የተፈጠረች ነች

ከሞት መነሳት

የምድር ዳርቻ

ርዕሶች የሚጻፉት በደማቅ ጽሁፍ ፊደሎች ናቸው።

ርዕሶቹም በተጨማሪ አጭር ትርጉም አላቸው።

አንዳንዶቹ ርዕሶች አነስተኛ ርዕሶች አሏቸው። እነዚህም ጠመም ባለ የፊደል አጣጣል የተጻፉ ናቸው።

ከእዚያ ርዕሶች ጋር የተያያዙ ቅዱሳት መጻህፍት ጥቅሶች በቅንፎች ውስጥ ይገኛሉ።

አንዳንዴም የርዕሱ መረጃ ከተመለከታችሁት ርዕስ በታች አይገኝም። ተመልከቱ የሚለው ቃል መረጃው ወደ ሚገኝበት ርዕስ ይመራችኋል።

አንዳንዴም በመመሪያው ውስጥ የሚገኙት ሌሎች ርዕሶች ከምታጠኑት ርዕስ ጋር የሚገናኙ መረጃዎችን የያዙ ይሆናሉ። ደግሞም…ተመልከቱ የሚሉት ቃላት ወደ ተገናኙት ርዕሶች ይመሯችኋል።

ትርጉሙ እንዲገባችሁ የሚያደርጉ የቅዱሳት መጻህፍት ጥቅሶችም በ ቅንፎች ውስጥ ይገኛሉ።

እያንዳንዱ የቅዱስ መፅሐፍ ጥቅስ በቅዱስ መፅሀፉ አጭር ጥቅስ ወይም የቅዱስ መፅሐፍ ማጠቃለያ አላቸው።

መስመር የሚከተለው ተመልከቱ (ወይም ደግሞም…ተመልከቱ) የሚለው ቃል መረጃው ታናሽ መግቢያ (“የአለም መጨረሻ”) በዋና ርዕሱ (“አለም”) ውስጥ እንደሚገኝ ይነግሯችኋል።