የጥናት እርዳታዎች
ዳዊት


ዳዊት

በብሉይ ኪዳን ውስጥ የጥንት እስራኤል ንጉስ።

ዳዊት የይሁዳ ጎሳ አባል የሆነው የእሴይ ልጅ ነበር። አንበሳ፣ ድብ፣ እና ፍልስጥኤማዊ የጌት ሰው ጎልያድን የገደለ ብርቱ ወጣት ነበር (፩ ሳሙ. ፲፯)። ዳዊት የእስራኤል ንጉስ እንዲሆን ተመርጦ ተቀባ። እንደ ሳኦል፣ በጎልማሳ ህይወቱ በክፉ ጥፋት ወንጀለኛ ነበር፣ ነገር ግን ሳኦል እንዳላደረገው እርሱ ለእውነተኛ ጸጸት ችሎታ ነበረው። ስለዚህ ከኦርዮ ግድያ በስተቀር ይቅርታን ለማግኘት ችሎ ነበር (ት. እና ቃ. ፻፴፪፥፴፱)። ህይወት በአራት ክፍሎች ለመከፋፈል ይችላሉ፥ (፩) እረኛ በነበረበት በቤተ ልሔም (፩ ሳሙ. ፲፮–፲፯)፣ (፪) በንጉስ ሳኦል ቤተመንግስት (፩ ሳሙ. ፲፰፥፩–፲፱፥፲፰)፣ (፫) እንደ ስደተኛ (፩ ሳሙ. ፲፱፥፲፰–፴፩፥፲፫፪ ሳሙ. ፩)፣ (፬) በኬብሮን ውስጥ እንደ ይሁዳ ንጉስ (፪ ሳሙ. ፪–፬)፣ እና በኋላም እንደ ሙሉ እስራኤል ንጉስ (፪ ሳሙ. ፭–፳፬፩ ነገሥ. ፩፥፩–፪፥፲፩)።

ዳዊት ከቤርሳቤህ ጋር በዝሙት የፈጸመው ኃጢያት የህይወቱን የመጨረሻ ሀያ አመትን ባጠፉበት መጥፎ እድሎች ተከታትለዋል። በንግስናው ዘመን ሀገሩ በሙሉ በልፅገው ነበር፣ ነገር ግን ዳዊት በኃጢያቶቹ ውጤቶች ምክንያት ተሰቃየ። ብዙ የቤተሰብ ጸብ ነበሩ፣ በዚህም አቤሴሎምና አዶንያስ በግልጽ አመጹ። እነዚህ ችግሮች ነቢዩ ናታን በዳዊት ላይ በኃጢያቶቹ ምክንያት ያስታወቃቸው የተሟሉበት ነበሩ (፪ ሳሙ. ፲፪፥፯–፲፫)።

እነዚህ ሀይለኛ ጥፋቶች ቢኖሩም፣ የዳዊት ግዛት በእስራኤላውያን ታሪክ ሁሉ በጣም አስደናቂ የነበረ ነው፣ ምክንያቱም (፩) ጎሳዎችን በአንድ ሀገር አስተባበራቸው፣ (፪) ሀገሩን ያለብጥበጣ ሀላፊነት ያዘ፣ (፫) መንግስትን በእውነተኛው ሀይማኖት ላይ በመመስረት የእግዚአብሔርን ፍላጎት የእስራኤል ህግ አደረገ። ለዚህ ምክንያት፣ በኋላም የዳዊት ግዛት የሀገሩ ወርቃማ ዘመን እና መሲህ በሚመጣበት ጊዜ እንደሚሆነው ግርማዊ እድሜ አይነት ምሳሌ እንደሆነ ታስቦበታል (ኢሳ. ፲፮፥፭ኤር. ፳፫፥፭ሕዝ. ፴፯፥፳፬–፳፰)።

የዳዊት ህይወት ሁሉም ሰዎች እስከ መጨረሻ በጻድቅ ለመፅናት አስፈላጊነትን የሚያሳይ ነበር። እንደ ወጣትነቱ፣ እርሱ “እግዚአብሔር እንደ ልቡ የሆነ ሰው” ነው ተብሎ ነበር (፩ ሳሙ. ፲፫፥፲፬)፤ እንደ ጎላምሳም፣ በመንፈስ ተናገረ እናም ብዙ ራዕያትም ነበሩት። ነገር ግን ለእግዚአብሔር ትእዛዛት ታዛዥ ባለመሆኑ ከባድ የሆነ የቅጣት ክፍያ ነበረበት (ት. እና ቃ. ፻፴፪፥፴፱)።