የጥናት እርዳታዎች
የጳውሎስ መልእክቶች


የጳውሎስ መልእክቶች

ጳውሎስ ለቤተክርስቲያኗ አባላት በመጀመሪያ የጻፋቸው ደብዳቤዎች የነበሩ የአዲስ ኪዳን አስራ አራት መፅሐፎች። እነዚህ በቡድኖች እንዲህ ለመከፋፈል ይችላሉ፥

፩ እና ፪ ተሰሎንቄ (፶–፶፩ ዓ.ም.)

ጳውሎስ መልእክቶችን ለተሰሎንቄ የጻፈው በሁለተኛው የሚስዮን ጉዞ ከቆሮንቶስ ነበር። በተሰሎንቄ የሰራው በሐዋርያት ስራ ፲፯ ውስጥ ተገልጿል። ወደ ተሰሎንቄ ለመመለስ ፈለገ፣ ነገር ግን አልቻለም (፩ ተሰ. ፪፥፲፰)። ስለዚህ ተቀያሪዎችን እንዲያስደስት እና እንዴት እንደሆኑ ዜና እንዲያመጣለት ጢሞቴዎስን ላከው። የመጀመሪያው መልእክት የጢሞቴዎስ በደህንነት መመለስ ምስጋና ውጤት ነው። ሁለተኛው መልእክት የተጻፈው ከእዚያ ጊዜ ከአጭር ጊዜ በኋላ ነበር።

፩ እና ፪ ቆሮንቶስ፣ ገላትያ፣ ሮሜ (በ፶፭–፶፯ ዓ.ም.)

ጳውሎስ በሶስተኛው የሚስዮን ጉዞው ለቆሮንቶስ ሰዎች መልእክቱን የጻፈው ጥያቄዎችን ለመመለስ እና በቆሮንቶስ ቅዱሳን መካከል ያለውን ስህተት ለማስተካከል ነበር።

ወደ ገላትያ ሰዎች የጻፈው መልእክት በገላትያ ውስጥ ለነበሩት ብዙ ቤተክርስቲያናት ይሆን ነበር። አንዳንድ የቤተክርስቲያን አባላት የአይሁዳ ህግን ለማክበር ወንጌሉን ትተው ይሄዱ ነበር። በእዚህ ደብዳቤ፣ ጳውሎስ የሙሴ ህግ አላማን እና የመንፈሳዊ ሀይማኖት ዋጋን ገለጸ።

ጳውሎስ ከቆሮንቶስ ወደ ሮሜ ሰዎች መልእክትን የጻፈው፣ እነርሱን ለመጎብኘት ተስፋ ለነበረው ጊዜ የሮሜ ቅዱሳንን ለማዘጋጀት ነበር። ደብዳቤው ደግሞም ወደ ክርስቲያንነት በተቀየሩ አንዳንድ አይሁዶች ይከራከሩበት የነበረውን ትምህርት ያረጋግጣል።

ፊልጵስዮስ፣ ቄላስይስ፣ ኤፌሶን፣ ፊልሞን፣ ዕብራውያን (፷–፷፪ ዓ.ም.)

ጳውሎስ እነዚህን መልእክቶች የጻፈው ለመጀመሪያ ጊዜ በሮሜ እስር ቤት ውስጥ በነበረበት ጊዜ ነበር።

ጳውሎስ ለፊልጵስዮስ መልእክቱን የጻፈው ለፊልጵስዮስ ሰዎች ያለውን ምስጋና እና ፍቅር ለመግለፅ እና ለብዙ ጊዜ በመታሰሩ ከነበራቸው የተስፋ መቁረጥ እነርሱን ለማስደሰት ነበር።

ጳውሎስ ወደ ቄላስይስ ሰዎች መልእክትን የላከው የቄላስይስ ቅዱሳን ወደ ከፍተኛ ስህተት እየሄዱ እንደሆኑ በደረሰው ዜና ምክንያት ነበር። ፍጹምነት የሚመጣው የክርስቶስ አይነት ጸባይ በማግኘት ሳይሆን የውጪ ስነስርዓቶችን በማከናወን ብቻ ነው ብለው ያምኑ ነበር።

ወደ ኤፌሶን ሰዎች መልእክቱ ስለክርስቶስ ቤተክርስቲያን ትምህርቶችን ስለያዘ በጣም አስፈላጊ ነበር።

ወደ ፊልሞን ሰዎች የላከው መልእክት ጌታውን ስለዘረፈው እና ወደ ሮሜ ስለሸሸው ባሪያ አናሲሞስ በሚመለከት ለፊልሞን የላከው የግል ደብዳቤ ነበር። ጳውሎስ አናሲሞስ ይቅርታ እንዲሰጠው በመጠየቅ አናሲሞስን ወደ ጌታው መልሶ ላከው።

ጳውሎስ ወደ ዕብራውያን የጻፈው መልእክት የቤተክርስቲያኗ የአይሁዳ አባላትን የሙሴ ህግ በክርስቶስ እንደተሟላ እና የክርስቶስ ወንጌል ይህን ተክቶ እንደመለሰው ለማሳመን ነበር።

፩ እና ፪ ጢሞቴዎስ፣ ቲቶ (፷፬–፷፭ ዓ.ም.)

ጳውሎስ እነዚህን መልእክቶች የጻፈው በመጀመሪያ ከሮሜ እስር ቤት ከተለቀቀ በኋላ ነበር።

ጳውሎስ ወደ ኤፌሶን ተጓዘ፣ በእዚያም ጢሞቴዎስን የትምህርት ግምቶችን እንዲያቆም ትቶት በኋላም ለመመለስ እያሰበ ሄደ። የመጀመሪያውን መልእክቱን፣ ምናልባት ከመቄዶንያ፣ ጢሞቴዎስን ለመምከር እና ሀላፊነቱን በማሟላት ለማበረታታት የጻፈው ነበር።

ጳውሎስ መልእክትን ወደ ቲቶ የላከው ከእስር ቤት በወጣበት ጊዜ ነበር። ቲቶ የሚያገለግልበትን ቀርጤስ ገንብቶም ይሆን ነበር። ደብዳቤው ስለጻድቅ ኑሮ እና ስለ ቤተክርስቲያኗ ውስጥ ስነስርዓት ነበር።

ጳውሎስ ለጢሞቴዎስ ሁለተኛውን ደብዳቤ የጻፈው፣ ከጳውሎስ ስማዕት አጭር ጊዜ በፊት፣ ለሁለተኛ ጊዜ በእስር ቤት ውስጥ እያለ ነበር። ይህ መልእክት የጳውሎስን የመጨረሻ ቃላት ይዟል እናም ሞትን በምን አይነት ጉብዝና እና እምነት እንደተቋቋመ ያሳያል።