የጥናት እርዳታዎች
ዮሴፍ፣ የያዕቆብ ልጅ


ዮሴፍ፣ የያዕቆብ ልጅ

በብሉይ ኪዳን ውስጥ፣ የያዕቆብ እና የራሔል በኩር ልጅ (ዘፍጥ. ፴፥፳፪–፳፬፴፯፥፫)።

ዮሴፍ የበኩር መብትን ያገኘው ከያዕቆብ የመጀመሪያ ባለቤት በኩል ልጅ ሮቤል መብቱን በመተላለፉ ምክንያት ስላጣ ነበር (፩ ዜና ፭፥፩–፪)። እርሱ ብቁ ስለነበረ፣ ዮሴፍ እንደ ያዕቆብ ሁለተኛ ባለቤት በኩል ልጅ፣ ለበረከቱ በተከታይነት መብት ነበረው። ያዕቆብ ከመሞቱ ከትንሽ ጊዜ በፊት፣ ዮሴፍ ከአባቱም በረከትን ተቀበለ (ዘፍጥ. ፵፱፥፳፪–፳፮)።

ዮሴፍ ታላቅ መንፈሰ ጠንካራነት ያለው፣ “ያለ ብልህ አዋቂም ሰው” ነበር (ዘፍጥ. ፵፩፥፴፱)። የጲጥፋራ ባለቤትን ማስወገዱ የእምነት፣ የንጹህነት እና የግለሰብ ታማኝነት ምሳሌ ነው (ዘፍጥ. ፴፱፥፯–፲፪)። በግብፅ ውስጥ፣ ጆሴፍ እውነተኛ ማንነቱን ለወንድሞቹ ሲገልፅ፣ ምንም ላደረጉበት እነርሱን ሳይወቅስ ምስጋና ሰጣቸው። ስራቸው የእግዚአብሔርን ፍቃድ ለማሟላት እንደረዳ አምኖ ነበር (ዘፍጥ. ፵፭፥፬–፲፭)።

የኋለኛው ቀን ራዕይ የጆሴፍ ቤተሰብ በኋለኛው ቀን ስላላቸው ታላቅ ተልዕኮ ገልጦአል (ጆ.ስ.ት.፣ ዘፍጥ. ፶፥፳፬–፴፰ [ተጨማሪ]፪ ኔፊ ፫፥፫–፳፬፫ ኔፊ ፳፥፳፭–፳፯)።