ክፍል ፺
በመጋቢት ፰፣ ፲፰፻፴፫ (እ.አ.አ.) በከርትላንድ ኦሀዮ ለነቢዩ ጆሴፍ ስሚዝ የተሰጠ ራዕይ። ይህ ራዕይ የቀዳሚ አመራርን ለመመስረት የቀጠለ እርምጃ ነው (የክፍል ፹፩ ርዕስን ተመልከቱ)፤ በዚህም ምክንያት፣ የተጠቀሱት አማካሪዎች በመጋቢት ፲፰፣ ፲፰፻፴፫ (እ.አ.አ.) ተሾሙ።
፩–፭፣ የመንግስት ቁልፎች ለጆሴፍ ስሚዝ እና በእርሱም በኩል ለቤተክርስቲያኗ ተሰጥተዋል፤ ፮–፯፣ ስድኒ ሪግደን እና ፍረድሪክ ጂ ዊሊያምስ በቀዳሚ አመራር ያገልግሉ፤ ፰–፲፩፣ ወንጌሉ ለእስራኤል ህዝብ፣ ለአህዛብ፣ እና ለአይሁድ፣ እያንዳንዱም ሰው በሚሰማው ቋንቋ ይሰበክለት፤ ፲፪–፲፰፣ ጆሴፍና አማካሪዎቹ ቤተክርስቲያኗን በስርዓት ያደራጁ፤ ፲፱–፴፯፣ የተለያዩ ግለሰቦች በቅንነት እንዲሄዱ እና በመንግስቱ እንዲያገለግሉ በጌታ ተመክረዋል።
፩ ጌታ እንዲህ ይላል፣ ልጄ ሆይ እውነት፣ እውነት እልሀለሁ፣ በልመናህ መሰረት፣ ኃጢአቶችህ ሀተሰርየውልሀል፣ የአንተ እና የወንድሞችህ ጸሎቶች ወደ ጆሮዎቼ መጥተዋልና።
፪ ስለዚህ፣ የተሰጠህን የመንግስት ሀቁልፎች ለመያዝ ከዚህ ጀምሮ ተባርከሀል፤ ይህም ለመንግስት ለመጨረሻ ጊዜ እየመጣ ያለው ነው።
፫ እውነት እልሀለሁ፣ በዚህ አለምም ሆነ በሚመጣው አለም ሳለህ፣ የመንግስት ቁልፎች ከአንተ በምንም መንገድ አይወሰድብህም፤
፬ ይህም ቢሆን፣ አዎን፣ በአንተ በኩል ሀየእግዚአብሔር ቃላት ለሌላ፣ እንዲሁም ለቤተክርስቲያኗ፣ ይሰጣሉ።
፭ እና የእግዚአብሔርን ቃላት የሚቀበሉ ሁሉ፣ እንደ ቀላል ነገር እንዳይቆጥሯቸው፣ እና በዚህም ፍርድ እንዳይመጣባቸው፣ እና ማእበሉ ሲወርድ፣ እና ነፋሱም ሲነፍስ፣ እና ሀዝናብም ሲጥል፣ እና ቤታቸውንም ሲገፋው እንዳይደናቀፉ እና እንዳይወድቁ፣ እንዴት እንደሚይዟቸው ለይጠንቀቁ።
፮ ደግሞም፣ ለወንድሞችህ ስድኒ ሪግደንና ፍረድሪክ ጂ ዊሊያም እውነት እላቸዋለሁ፣ ኃጢአቶቻቸውም ደግሞ ተሰርየዋል፣ እና የዚህን የመጨረሻ መንግስት ቁልፎችን መያዝን በተመለከተ ከአንተ ጋር እንደ እኩል ይቆጠራሉ፣
፯ ደግሞም እንዲደራጅ ያዘዝኩትን የነብያት ሀትምህርት ቤት ማስተዳደሪያ ቁልፎችን መያዝን በተመለከተ ከአንተ ጋር እንደ እኩል ይቆጠራሉ፤
፰ በዚህም፣ የሚያምኑት ሁሉ፣ ለፅዮን፣ እና ለእስራኤል ህዝብ፣ እና ለአህዛብ ደህንነት በአገለግሎታቸው ፍጹማን ይሆኑ ዘንድ፤
፱ በአገልግሎትህ ቃልን ይቀበሉ ዘንድ፣ እና በአገልግሎታቸውም ቃል፣ እስከ ምድር ዳርቻ ይሄድ ዘንድ፤ ሀመጀመሪያ ወደ ለአህዛብ፣ እና ከዚያም እነሆ አስተውሉ፣ ወደ አይሁድም ይዞራሉ።
፲ ከዚያም ህዝብን፣ የአህዛብን አገሮች፣ ሀየጆሴፍን ቤት፣ የደህንነታቸውን ወንጌል ለማሳመን የጌታ እጅ በሀይል ለየሚገለጥበት ቀን ይመጣል።
፲፩ በዚያም ቀን እንዲህ ይሆናል፣ የወንጌል ሙላትን ለዚህ ሀሀይል ለበተሾሙት በኩል፣ የኢየሱስ ክርስቶስ ራዕይ በሚፈስባቸው ሐበአፅናኙ አገልግሎት፣ እያንዳንዱ ሰው በገዛ ልሳን እና በራሱ ቋንቋ መይሰማል።
፲፪ አሁንም፣ እውነት እላችኋለሁ፣ ሀበአገልግሎቱ እና በአመራሩ እንድትቀጥሉ ትእዛዝ እሰጣችኋለሁ።
፲፫ እና የነቢያትን ትርጉም ስትጨርሱ፣ ከዚህ በኋላ የቤተክርስቲያኗን እና ሀየትምህርት ቤቱን ጉዳዮች ለትመራላችሁ፤
፲፬ እና ከጊዜ ወደ ጊዜም፣ በአፅናኙ እንደሚገለጸው፣ ተነግረው የማይታወቁ የመንግስትን ሀሚስጥራት ለበራዕይ ተቀበሉ፤
፲፭ እና ቤተክርስቲያኖችንም በስርዓት አደራጁ፣ እና ሀአጥኑና ለተማሩ፣ እና ሁሉንም መልካም መጻህፍት፣ ሐቋንቋዎች፣ ልሳኖች፣ እና ህዝብን እወቁ።
፲፮ እና ይህም፣ ኮሚቴውን መምራት፣ እና የዚህን ቤተክርስቲያን እና መንግስት ጉዳዮች በስርዓት ማደራጀት፣ በህይወታችሁ ሁሉ ጉዳያችሁ እና ተልዕኮአችሁ ይሆናል።
፲፯ ሀአትፈሩ፣ ወይም አትዋረዱ፤ ነገር ግን በትዕቢታችሁ እና ለበኩራታችሁም ተገሰጹ፣ በነፍሶቻችሁ ወጥመድ ያመጣልና።
፲፰ ቤቶቻችሁንም በስርዓት አስተካክሉ፤ ሀስራ ፈትነትን እና ለጽዱ አለመሆንን ከእናንተ አርቁ።
፲፱ አሁን፣ እውነት እልሀለሁ፣ ወድያውኑ ሲቻል፣ ለአማካሪህ እና ለጸሀፊህ፣ እንዲሁም ለፍረድሪክ ጂ ዊሊያምስ ቤተሰብ ስፍራ ይሰጥ።
፳ እና አዛውንቱ አገልጋዬ፣ ሀጆሴፍ ስሚዝ፣ ቀዳማዊም፣ አሁን በሚኖርበት ስፍራ ከቤተሰቡ ጋር ይቀጥል፤ እና የጌታ አንደበት እስከሚወስንበትም ድረስ አይሸጥ።
፳፩ እና አማካሪዬ፣ እንዲሁም ሀስድኒ ሪግደን፣ የጌታ አንደበት እስከሚወስንበት ድረስ አሁን በሚኖርበት ይቆይ።
፳፪ እና ኤጲስ ቆጶሱ በቅንነት ሀወኪልን ለማግኘት ይፈልግ፣ እና ይህም ሰው ለሀብት ያከማቸ፣ የእግዚአብሔር ሰው፣ እና ጠንካራ እምነት ያለው ይሁን—
፳፫ በዚህም እያንዳንዱን እዳ ለመክፈል ችሎታ ይኖረው ዘንድ፤ የጌታ ጎተራ በሰዎቹ አይኖች ፊት መጥፎ ስም አይኖረው ዘንድ ወኪሉ ሀብት ያከማቸ የእግዚአብሔር ሰው፣ እና ጠንካራ እምነት ያለው ይሁን።
፳፬ ሀተግታችሁ ፈልጉ፣ ዘወትር ለጸልዩ፣ እናም እመኑ፣ እና በቅንነት ከተራመዳችሁ እና እርስ በራስ ቃል ኪዳን የገባችሁበትን ሐቃል ኪዳን ካስታወሳችሁ፣ መሁሉም ነገሮች ለእናንተ በጎነት አብረው ይሰራሉ።
፳፭ ሀቤተሰቦቻችሁ አነስተኛ ይሁኑ፤ በተለይም የቤተሰባችሁ አባል ያልሆኑትን በሚመለከት፤ በተለይም የአዛውንቱ ጆሴፍ ስሚዝ፣ ቀዳማዊ ቤተሰብም፤
፳፮ ስራዎቼ እንዲከናወኑ፣ ለእናንተ የተሰጧችሁ ነገሮች ከእናንተ እንዳይወሰዱ እና ብቁ ላልሆኑት እንዳይሰጥ ዘንድ—
፳፯ እና በዚህም ያዘዝኳችሁን ነገሮች ለማከናወን እንዳትደናቀፉ ቤተሰቦቻችሁ አነስተኛ ይሁኑ።
፳፰ ደግሜ፣ እውነት እላችኋለሁ፣ ባሪያዬ ቪየና ዣክ ወጪዋን እንድትችል፣ እና ወደ ፅዮን ምድር ለመሄድ ገንዘብ ይሰጣት ዘንድ ፍቃዴ ነው፤
፳፱ እና የሚቀረው ገንዘብም ለእኔ ይቀደስ፣ እና በጊዜዬም ዋጋዋን ታገኛለች።
፴ እውነት እላችኋለሁ፣ ወደ ፅዮን ምድር እንድትሄድ፣ እና ከኤጲስ ቆጶስ እጅ ውርሷን እንድትቀበል ፍቃዴ ነው፤
፴፩ ታማኝ እስከሆነች ድረስ በሰላም እንድትሰፍር፣ እና ከዚህ በኋላ በቀኖቿ ስራ ፈት እንዳትሆን ፍቃዴ ነው።
፴፪ እነሆም፣ እውነት እላችኋለሁ፣ ይህን ትእዛዝ ጻፉ፣ እና በፅዮን ውስጥ ያሉ ወንድሞቻችሁን፣ በፍቅር ሰላምታ፣ በጊዜዬ በፅዮን ሀእንድትመሩ እንደተጠራችሁ ንገሯቸው።
፴፫ ስለዚህ፣ በዚህ ጉዳይ እኔን ማድከማቸውን ያቁሙ።
፴፬ እነሆ፣ እላችኋለሁ በፅዮን ያሉት ወንድሞቻችሁ ንስሀ ይግቡ፣ እና መላእክት በእነርሱ ይደሰቱ።
፴፭ ይህም ቢሆን፣ በብዙ ነገሮች አልተደሰትኩም፤ እና በአገልጋዬ ሀዊሊያም ኢ መክሌይን፣ ወይም በአገልጋዬ ስድኒ ጊልበርት አልተደሰትኩም፤ እና ኤጲስ ቆጶሱና ሌሎች ንስሀ የሚገቡበት ብዙ ነገሮች አላቸው።
፴፮ ነገር ግን እውነት እላችኋለሁ እኔ ጌታ ሀከፅዮን ጋር እጣላለሁ፣ እና ጠንካራዋን ለምኛለሁ፣ እና እስክትሸነፍ እና በፊቴ ለንጹህ እስክትሆን ድረስ ሐእገስጻለሁ።
፴፯ ከስፍራዋ ልትነቃነቅ አትችልምና። እኔ ጌታ ተናግሬዋለሁ። አሜን።