ክፍል ፬
የካቲት ፲፰፻፳፱ (እ.አ.አ.) በሀርመኒ ፔንስልቬንያ፣ በነቢዩ ጆሴፍ ስሚዝ በኩል ለአባቱ ለጆሴፍ ስሚዝ ቀዳማዊ የተሰጠ ራዕይ።
፩–፬፣ የጌታን አገልጋዮች የጀግና አገልግሎት ያድናቸዋል፤ ፭–፮፣ አምላካዊ ባህሪያት ላገልግሎቱ ብቁ ያደርጋቸዋል፤ ፯፣ የእግዚአብሔር ነገሮች መሻት አለባቸው።
፩ አሁን እነሆ፣ በሰዎች ልጆች መካከል ሀድንቅ ስራ ሊመጣ ነው።
፪ ስለዚህ እናንት በእግዚአብሔር ሀአገልግሎት ውስጥ መሳተፍ የጀመራችሁ፤ በመጨረሻው ቀን በእግዚአብሔር ፊት ለያለወቀሳ ትቆሙ ዘንድ፣ በሙሉ ሐልባችሁ፤ ኃይላችሁ፣ አዕምሮአችሁ እና ጉልበታችሁ መእንደምታገለግሉት አረጋግጡ።
፫ ስለዚህ፣ እግዚአብሔርን ለማገልገል ፈቃድ ካላችሁ ወደስራው ሀተጠርታችኋል፤
፬ ስለሆነም እነሆ ሀእርሻው ነጥቷል ለአዝመራውም ዝግጁ ነው፤ እናም አስተውሉ፣ በጥንካሬው የሚያጭድ እንዳይጠፋ ዘንድ ሐበጎተራው ይከምራል፣ ነገር ግን ለነፍሱ ደህንነትን ያመጣል፤
፭ እናም ሀእምነት፣ ለተስፋ፣ ሐለጋስነትና መፍቅር፣ ሙሉ ሠአይኑን ወደ እግዚአብሔር ረክብር ከማድረግ ጋር ለስራ ብቁ ያደርጉታል።
፮ እምነት፣ ሀምግባረ በጎነት፣ ዕውቀት፣ ራስን መግዛት፣ ለትዕግስት፣ ወንድማዊ ደግነት፣ አምላካዊነት፣ ልግስና፣ ሐትህትና፣ መትጋትን አስታውሱ።
፯ ሀለምኑ፣ እናም ይሰጣችኋል፤ አንኳኩ፣ ይከፈትላችኋል። አሜን።