ቅዱሳት መጻህፍት
ትምህርት እና ቃል ኪዳኖች ፵፬


ክፍል ፵፬

በየካቲት መጨረሻ አካባቢ፣ በ፲፰፻፴፩ (እ.አ.አ.) ለነቢዩ ጆሴፍ ስሚዝ እና ለስድኒ ሪግደን የተሰጠ ራዕይ። በዚህ ውስጥ የቀረቡትን ትእዛዛት በማክበር፣ ቤተክርስቲያኗ በሚቀጥለው ሰኔ መጀመሪያ ላይ ጉባኤ እንዲኖር መደበች።

፩–፫፣ ሽማግሌዎች በጉባኤ ይሰብሰቡ፤ ፬–፮፣ በምድሪቷ ህግጋት መሰረት እናም ደሆችንም ይንከባከቡ ዘንድ ራሳቸውን ያደራጁ።

እነሆ፣ ጌታ ለእናንተ ለአገልጋዮቼ እንዲህ ይላል፣ የቤተክርስቲያኔ ሽማግሌዎች ከምስራቅና ከምእራብ፣ ከሰሜንና ከደቡብ፣ በደብዳቤ ወይም በሌላ መንገድ፣ መሰብሰባቸው ፍቃዴ ነው።

እናም እንዲህ ይሆናል ያልፋል፣ ታማኝ ቢሆኑ፣ እና በእኔም ያላቸውን እምነት ቢጠቀሙ፣ ራሳቸውን በሚሰበስቡበት ቀን መንፈሴን አፈስባቸዋለሁ።

እናም እንዲህ ይሆናል በአካባቢው ክፍለ ሀገሮች ይሂዱ፣ እና ለህዝቡ ንስሀን መግባትን ይስበኩ

እና፤ እንዲህም ሆኖ በሰው ህግጋት መሰረት ራሳችሁን ለማደራጀት ሀይልን እስካገኛችሁ ድረስ ብዙዎች ይለወጣሉ

ጠላቶቻችሁ በእናንተ ላይ ስልጣን እንዳይኖራቸው በሁሉም ነገሮች እንድትጠበቁ፣ ህግጋቴንም ለመጠበቅ እንድትችሉ፣ ጠላትም ህዝቤን ለማጥፋት የሚሻባቸው ስምምነቶች ይሰበሩ ዘንድ ራሳችሁን ለማደራጀት ሀይል ታገኛላችሁ።

እነሆ፣ እላችኋለሁ፣ ሁሉም ነገሮች በተቀበላችሁት ህጌ መሰረት እስከሚከናወኑ ድረስ ይጠበቁ ዘንድ፣ ደሆችንና ችግረኞችን ተንከባከቡ እና በሚያስፈልጋቸውም ነገሮች አገልግሏቸው። አሜን።