ክፍል ፻፳፭
በመጋቢት ፲፰፻፵፩ (እ.አ.አ.)፣ በናቩ ኢለኖይ ውስጥ በአየዋ ክልል ውስጥ ያሉትን ቅዱሳን በሚመለከት ለነቢዩ ጆሴፍ ስሚዝ የተሰጠ ራዕይ።
፩–፬፣ ቅዱሳን ከተማዎችን ይስሩ እና የፅዮን ካስማዎችንም ይሰብስቡ።
፩ በአየዋ ክልል ያሉትን ቅዱሳን በሚመለከት የጌታ ፈቃድ ምንድን ነው?
፪ ጌታ እንዲህ ይላል፣ እውነት እላችኋለሁ ሀበስሜ ራሳቸውን የሚጠሩና ቅዱሳኔ ለመሆን የሚጥሩ፣ የምፈልገውን ቢያደርጉ እና እነርሱን የሚመለከቱ ትእዛዛቴን ቢያከብሩ፣ በአገልጋዬ ጆሴፍ በምመድብላቸው ስፍራዎች ራሳቸውን አብረው ይሰብስቡ፣ እና ለሚመጣው ዘመንም ይዘጋጁ ዘንድ በስሜም ከተማዎችን ይስሩ።
፫ ከናቩ ከተማ የተለየ ከተማ በስሜ ይስሩ፣ እና ስሙም ሀዛራሔምላ ይሁን።
፬ እና በዚህ ውስጥ ለመኖር ፈቃድ ኖሮአቸው ከምስራቅ፣ እና ከምዕራብ፣ እና ከሰሜን፣ እና ከደቡብ የመጡት ሁሉ፣ ከዚህ፣ እና ሀከናሽቪል ከተማ፣ ወይም ከናቩ ከተማ፣ ከመደብኳቸው ለካስማዎች ሁሉ ውርሶቻቸውን ያግኙ፣ ይላል ጌታ።