ክፍል ፸፱
በመጋቢት ፲፪፣ ፲፰፻፴፪ (እ.አ.አ.) በሀይረም ኦሀዮ ውስጥ፣ በነቢዩ ጆሴፍ ስሚዝ በኩል የተሰጠ ራዕይ።
፩–፬፣ ጄርድ ካርተር በአፅናኙ ወንጌልን እንዲሰብክ ተጠርቷል።
፩ በእውነት እልሀለሁ፣ አገልጋዬ ጄሪድ ካርተር ዳግም ወደ ምስራቅ አገሮች፣ ከስፍራ ወደ ስፍራ፣ እናም ከከተማ ወደ ከተማ፣ ሀበተሾመበት ሹመት ሀይል ውስጥ ታላቅ ደስታ የምስራች፣ እንዲሁም ዘለአለማዊ ወንጌልን፣ እየሰበከ እንዲሄድ ፍቃዴ ነው።
፪ እናም እውነትን እና የሚሄድበትን መንገድ የሚያስተምረውን ሀአፅናኝንም እልክለታለሁ፤
፫ እናም የታመነ ቢሆን፣ ደግሞም በነዶም አነግሰዋለሁ።
፬ ስለዚህ፣ ልብህ ይደሰት፣ አገልጋዬ ጄርድ ካርተር፣ እናም ሀአትፍራ፣ ይላል ጌታህ፣ እንዲሁም ኢየሱስ ክርስቶስ። አሜን።