ቅዱሳት መጻህፍት
ትምህርት እና ቃል ኪዳኖች ፲፮


ክፍል ፲፮

ሰኔ ፲፰፻፳፱ (እ.አ.አ.) በፈየት፣ ኒው ዮርክ፣ በነቢዩ ጆሴፍ ስሚዝ አማካይነት ለፒተር ዊትመር ዳግማዊ፣ የተሰጠ ራዕይ። (የክፍል ፲፬ ርዕስን ተመልከቱ)። በኋላም ፒተር ዊትመር ዳግማዊ ከስምንቶቹ አንዱ የመፅሐፈ ሞርሞን ምስክር ሆነ።

፩–፪፣ የጌታ ክንድ በምድር ላይ ሁሉ ነው፤ ፫–፮፣ ወንጌልን መስበክ እና ነፍሳትን ማዳን ታላቅ ዋጋ ያለው ነገር ነው።

አድምጥ፣ አገልጋዬ ፒተር እናም የጌታህን እና የአዳኝህን የኢየሱስ ክርስቶስን ቃላት አድምጥ።

ስለሆነም እነሆ፣ ክንዴ በምድር ሁሉ ላይ ስለሆነ፣ በስልጣን እና በሀይል እናገርሀለሁ።

ከእኔ እና ከአንተ ብቻ በቀር ማንም ሰው የማያውቀውን ነገር እነግርሀለሁ—

ስለሆነ ብዙ ጊዜ ለአንተ ትልቅ ዋጋ ያለው ነገር ምን እንደሆነ ከእኔ ለማወቅ ፈልገሀል።

እነሆ፣ ስለ እነዚህ ነገሮች፣ እናም የሰጠሁህን ቃላቴን በትእዛዛቴ መሰረት ስለተናገርክ የተባረክ ነህ።

እናም አሁን፣ እነሆ እንዲህ እልሀለሁ፣ ለአንተ ታላቅ ዋጋ ያለው፣ ነፍሳትን ወደ እኔ ታመጣ ዘንድ፣ ከእነርሱ ጋር በአባቴ መንግስት ታርፍ ዘንድ፣ ለዚህ ህዝብ ንስሀን ማወጅ ይሆናል። አሜን።