ቅዱሳት መጻህፍት
ትምህርት እና ቃል ኪዳኖች ፲፭


ክፍል ፲፭

ሰኔ ፲፰፻፳፱ (እ.አ.አ.) በፈየት፣ ኒው ዮርክ፣ በነቢዩ ጆሴፍ ስሚዝ አማካይነት ለጆን ዊትመር የተሰጠ ራዕይ (የክፍል ፲፬ ርዕስን ተመልከቱ)። ይህ በቅርበት እና በሚገርም ሁኔታ የግል መልዕክት ነው፣ ጌታ በጆን ዊትመር እና በራሱ ብቻ የሚታወቀውን ይናገራል። ጆን ዊትመር በኋላም ከስምንቶቹ አንዱ የመፅሐፈ ሞርሞን ምስክር ሆነ።

፩–፪፣ የጌታ ክንድ በምድር ላይ ሁሉ ነው፤ ፫–፮፣ ወንጌልን መስበክ እና ነፍሳትን ማዳን ታላቅ ዋጋ ያለው ነገር ነው።

አድምጥ፣ አገልጋዬ ጆን እናም የጌታህን እና የአዳኝህን የኢየሱስ ክርስቶስን ቃላት አድምጥ።

ስለሆነም እነሆ፣ ክንዴ በምድር ሁሉ ላይ ስለሆነ፣ በስልጣን እና በሀይል እናገርሀለሁ።

እናም ከእኔ እና ከአንተ ብቻ በቀር ማንም ሰው የማያውቀውን ነገር እነግርሀለሁ—

ስለሆነ ብዙ ጊዜ ላንተ ትልቅ ዋጋ ያለው ነገር ምን እንደሆነ ከእኔ ለማወቅ ፈልገሀል።

እነሆ፣ ስለ እነዚህ ነገሮች፣ እናም የሰጠሁህን ቃላቴን በትእዛዛቴ መሰረት ስለተናገርህ የተባረክ ነህ።

እናም አሁን፣ እነሆ፣ እንዲህ እልሀለሁ፣ ለአንተ ታላቅ ዋጋ ያለው ነገር፣ ነፍሳትን ወደ እኔ ታመጣ ዘንድ ከእነርሱም ጋር በአባቴ መንግስት ታርፍ ዘንድ ለዚህ ህዝብ ንስሀን ማወጅ ይሆናል። አሜን።