ክፍል ፱
ሚያዚያ ፲፰፻፳፱ (እ.አ.አ.) በሀርመኒ፣ ፔንስልቬንያ፣ በነቢዩ ጆሴፍ ስሚዝ አማካይነት ለኦሊቨር ካውድሪ የተሰጠ ራዕይ። ኦሊቨር ትዕግስተኛ እንዲሆን ተገሰጸ እናም ለመተርጎም ከመሞከር ይልቅ ለጊዜው የተርጓሚውን ቃላት በመጻፍ እንዲደሰት ተመከረ።
፩–፮፣ ሌሎች ጥንታዊ መዛግብት ገና ይተርጎማሉ፤ ፯–፲፬፣ መፅሐፈ ሞርሞን በጥናት እና በመንፈሳዊ ማረጋገጫ ተተረጎመ።
፩ እነሆ፣ ልጄ ሆይ እንዲህ እልሀለሁ፣ ከእኔ በፈለከው መሰረት ሀስላልተረጎምህ እናም ዳግም ለአገልጋዬ፣ ለጆሴፍ ስሚዝ፣ ዳግማዊ ለመጻፍን በመጀመርህ ምክንያት በእርሱ ላይ እምነት የጣልኩበትን መዝገብ እስክትጨርስ ድረስ እንድትቀጥል እፈልጋለሁ።
፪ እና ከዚያም እነሆ፣ ሀሌሎች ለመዛግብቶች አሉኝ፣ ያንንም በመተርጎም እንድትረዳ ኃይል እሰጥኃለሁ።
፫ ልጄ ትዕግስተኛ ሁን፣ ይህ በእኔ ዘንድ ጥበብ ነውና፣ እናም በአሁኑ ጊዜ መተርጎምህ አስፈላጊ አይደለም።
፬ እነሆ፣ እንድታደርገው የተጠራህበት ስራ ለአገልጋዬ ለጆሴፍ እንድትጽፍ ነው።
፭ እናም፣ እነሆ፣ ይህንም እድል ከአንተ የወሰድኩብህ መተርጎም በጀመርህ ጊዜ እንደ ጀመርኸው ባለመቀጠልህ ምክንያት ነው።
፮ ሀአታጉረምርም፣ ልጄ ሆይ፣ ከአንተ ጋር በዚህ ሁኔታ ይህን ማድርጌ ጥበብ ነው።
፯ እነሆ፣ አልተረዳህም፤ እኔን ከመጠይቅህ በስተቀር ምንም ሳታስብበት፣ እንደምሰጥህ ገምተህ ነበር።
፰ ነገር ግን እነሆ፣ እንዲህ እልሀለሁ፣ በአእምሮህ ውስጥ ሀልታጠናው ይገባል፤ ከዚያም ትክክለኛ መሆኑን ለልትጠይቀኝ ይገባል፣ እናም ትክክለኛ ከሆነ ሐውስጥህም መእንዲቃጠል አደርጋለሁ፤ ትክክል እንደሆነም ሠይሰማሀል።
፱ ነገር ግን ትክክል ካልሆነ እንደዚህ ያሉ ስሜቶች አይሰሙህም፣ ነገር ግን የተሳሳተ ነገርን የሚያስረሳ ሀየሀሳብ ብዥታ ይሆንልሀል፤ ስለዚህ፣ ከእኔ ካልተሰጠ በስተቀር ቅዱስ የሆነውን መጻፍ አትችልም።
፲ አሁን፣ ይህን አውቀህ ቢሆን ኖሮ ሀመተርጎም በቻልህ ነበር፤ ሆኖም፣ አሁን መተርጎምህ አስፈላጊ አይደለም።
፲፩ እነሆ፣ በጀመርህበት ጊዜ አስፈላጊ ነበር፤ ነገር ግን ሀፈራህ፣ እናም ጊዜውም አለፈ፣ እናም አሁን አስፈላጊ አይደለም፤
፲፪ የጠፋውን ጊዜ ለመተካት ለአገልጋዬ ሀጆሴፍ በቂ ጥንካሬን አብጅቼ እንደሰጠሁት አታይምን? እናም ማናችሁንም ቢሆን አልኮነንኩም።
፲፫ እንድታደርግ ያዘዝኩህን አድርግ፣ እናም ትበለጽጋለህ። ታማኝ ሁን፣ እናም ሀለፈተና ራስህን አታጋልጥ።
፲፬ አንተን ሀለጠራሁበት ለስራ ጸንተህ ቁም፣ እናም ከራስ ጠጉርህ አንዲት አትጠፋም፣ እናም በመጨረሻውም ቀን ሐከፍ ትላለህ። አሜን።