ክፍል ፯
ሚያዚያ ፲፰፻፳፱ (እ.አ.አ.) በሀርመኒ፣ ፔንስልቬንያ፣ ነቢዩ ጆሴፍ ስሚዝና ኦሊቨር ካውድሪ በኡሪምና ቱሚም ተወዳጁ ደቀመዝሙር ዮሐንስ በስጋ መኖርና አለመኖርን በተመለከተ ለጠየቁት ጥያቄ የተሰጠ ራዕይ። ይህ ራዕይ በዮሐንስ በብራና ላይ ተጽፎ በራሱ ተደብቆ ከነበረው ጽሁፍ ላይ የተተረጎመው ነው።
፩–፫፣ የተወደደው ዮሐንስ እስከ ጌታ ምፅዓት ድረስ ይኖራል፤ ፬–፰፣ ጴጥሮስ፣ ያዕቆብ፣ እና ዮሐንስ የወንጌልን ቁልፍ ይዘዋል።
፩ እናም ጌታ እንዲህ ሲል ተናገረኝ፥ የምወድህ ሀዮሐንስ ሆይ፣ ምንን ለትሻለህ? የፈለግኸውን ብትጠይቅ እሱም ይሰጥኃል።
፪ እናም እኔም እንዲህ አልኩት፥ ጌታ እንድኖርና ነፍሳትን ወደ አንተ እንዳመጣ ሀበሞት ላይ ስልጣንን ስጠኝ አልኩት።
፫ እናም ጌታም እንዲህ ይላልኝ፥ እውነት፣ እውነት፣ እልሀለሁ፣ ይህንን ስለፈለግህ እኔ ሀበክብር እስክመጣ ድረስ ለትኖራለህ እናም በሀገሮች፣ በነገዶች፣ በቋንቋዎች፣ እና በህዝብም ፊት ሐትተነብያለህ።
፬ በዚህም ምክንያት ጌታ ጴጥሮስን እንዲህ ይላልው፥ እኔ እስክመጣ እንዲኖር ብፈቅድ ያ ለአንተ ምንድን ነው? እርሱ ወደ እኔ ነፍሳትን ለማምጣት ፈልጓል፣ ነገር ግን አንተ በቶሎ ወደ እኔ ሀበመንግስቴ መምጣትን ፈልገሀል።
፭ ጴጥሮስምሆይ ለአንተ እንዲህ እልሀለሁ፣ ይህ መልካም ፈቃድ ነበር፤ ነገር ግን የምወደው እርሱ ተጨማሪ፣ ወይም ቀደም ብሎ ካደረገው የበለጠ ስራ በሰዎች መካከል ያደርግ ዘንድ ፈለገ።
፮ አዎን፣ ታላቅ የሆነን ስራ ወስዷል፤ ስለዚህ እንደነበልባል እሳት እና እንደ ሀአገልጋይ መልአክ አደርገዋለሁ፤ እርሱም ለበምድር ለሚኖሩ የደህንነት ሐወራሾችን ያገለግላል።
፯ እናም ለእርሱና ለወንድምህ ለያዕቆብ እንድታገለግል አደርግሀለሁ፤ እናም ለእናንተ ለሶስታችሁም እኔ እስክመጣ ድረስ ይህን ስልጣን እና የአገልግሎቱን ሀቁልፍ እሰጣችኋለሁ።
፰ እውነት እላችኋለሁ፣ ሁለታችሁም እንደመሻታችሁ ይሆንላችኋል፤ ሁለታችሁም በፈለጋችሁት ነገሮች ሀትደሰታላችሁና።