ቅዱሳት መጻህፍት
ትምህርት እና ቃል ኪዳኖች ፻፳፮


ክፍል ፻፳፮

በሐምሌ ፱፣ ፲፰፻፵፩ (እ.አ.አ.) በብሪገም ያንግ ቤት ውስጥ በነቢዩ ጆሴፍ ስሚዝ በኩል የተሰጠ ራዕይ። በዚህ ጊዜ ብሪገም ያንግ የአስራ ሑለቱ ሐዋርያት ቡድን ፕሬዘደንት ነበር።

፩–፫፣ ብሪገም ያንግ ለአገልግሎቱ ተሞግሷል እና ወደፊትም ወደውጪ ከመጓዝ ፋታን አገኘ።

ውድ እና ተወዳጅ ወንድም ብሪገም ያንግ፣ እውነት ጌታ እንዲህ ይልሀል፥ አገልጋዬ ብሪገም፣ እንዳለፉት ጊዜያት ቤተሰብህን እንድትተው አይጠበቅብህም፣ መስዋዕትህ በእኔ ዘንድ ተቀባይነትን አግኝቷልና።

ስለስሜም በጉዞዎችህ ከባድ ስራህን እና አገልግሎትህን አይቻለሁ።

ስለዚህ ቃሌን ወደውጪ እንድትልክ፣ እና ከዚህ ጊዜ ጀምሮ እስከ ዘለአለም ቤተሰብህን በልዩ ሁኔታ እንድትንከባከባቸው አዝሀለሁ። አሜን።