በቅዱሳት መጻሕፍት ውስጥ የሚገኙ ታሪኮች
የያናጊዳ ቤተሰብ


“የያናጊዳ ቤተሰብ፣” የትምህርት እና ቃል ኪዳኖች ታሪኮች [2024 (እ.አ.አ)]

“የያናጊዳ ቤተሰብ፣” የትምህርት እና ቃል ኪዳኖች ታሪኮች

1950–1951 (እ.አ.አ)

የያናጊዳ ቤተሰብ

አስራት እና በኢየሱስ ክርስቶስ ማመን

ቶሺኮ እና ቶኪቺ ያናጊዳ ከቤተሰባቸው ጋር።

ቶሺኮ እና ቶኪቺ ያናጊዳ በጃፓን ይኖሩ ነበር። በኢየሱስ ክርስቶስ አምነው በእርሱ ቤተክርስቲያን ተቀላቀሉ። ነገር ግን በዚያን ጊዜ ሕይወት በጃፓን ውስጥ አስቸጋሪ ነበር። ጦርነት ብዙ ቤቶችን እና ሕንፃዎችን አውድሞ ነበር። ቶሺኮ እና ቶኪቺ ለቤተሰባቸው ቤት መገንባት ፈልገው ነበር፣ ነገር ግን በጣም ድሆች ነበሩ።

ቅዱሳን3፥543

የያናጊዳ ቤተሰብ ከቤተክርስቲያኗ ሚስዮናውያን ጋር ሲነጋገሩ።

የያናጊዳ ቤተሰብ ጌታ አስራት እንዲከፍሉ እንደሚፈልግ ያውቁ ነበር፣ ነገር ግን ይህን ለማድረግ እንደሚችሉ እርግጠኞች አልነበሩም። ቶሺኮ አንድን ሚስዮናዊውን ምን ማድረግ እንዳለባቸው ጠየቀ። “አሥራት መክፈል ለእኛ በጣም ከባድ ነው” አለች። ሚስዮናዊው አስራት ከከፈሉ ቤት የመግዛት ግባቸው ላይ እንዲደርሱ ጌታ እንደሚረዳቸው ቃል ገባላቸው።

ትምህርት እና ቃል ኪዳኖች 119ቅዱሳን3፥543–44

ቶሺኮ እና ቶኪቺ አስራት መክፈል እንደሚቀጥሉ ወሰኑ።

ቶሺኮ እና ቶኪቺ እርግጠኞች አልነበሩም። ለልጃቸው የትምህርት ቤት ምሳ እንኳን የሚገዙበት በቂ ገንዘብ አልነበራቸውም። ነገር ግን በጌታ በመታመን አሥራትን ለመክፈል ወሰኑ።

ቅዱሳን3፥543–44

የያናጊዳ ቤተሰብ የወደፊት ቤታቸው በሚገነባበት ቦታ አጠገብ ቆመው።

ጌታ የያናጊዳ ቤተሰብን ባረከ። ብዙም ሳይቆይ መሬት ገዝተው ቤት መገንባት ጀመሩ።

ቅዱሳን3፥544

አንድ የግንባታ ሰራተኛ ቤታቸው ሊሰራ እንደማይችል ለያናጊዳ ቤተሰብ እየነገራቸው።

አንድ ቀን አንድ ተቆጣጣሪ መጣ። በመሬታቸው ላይ ችግር እንዳለ እና በእዚያ ቦታ ቤት መሥራት እንደማይችሉ ነገራቸው። ሰራተኞቹም እንዳይገነቡ አስቆማቸው።

ቅዱሳን3፥544

ከሚስዮኖች አንዱ ከቤተሰቡ ጋር እየተነጋገረ።

የያናጊዳ ቤተሰብ በጣም አዘኑ። የሆነውን ሁሉ ለሚስዮኖች ነገሩ። ሚስዮኖች ከያናጊዳ ቤተሰብ ጋር እንደሚጾሙ እና እንደሚጸልዩ ተናገሩ።

ቅዱሳን3፥545

የቤተሰብ ቤት ግንባታ እንደገና እየተጀመረ።

በኋላ ሌላ ተቆጣጣሪ መጣ። በመሬታቸው ላይ ያለው ችግር ሊስተካከል ይችላል አለ። የያናጊዳ ቤተሰብ ቤታቸውን መገንባት ይችላሉ። ተቆጣጣሪው ቶሺኮ እና ቶኪቺን “ሁለታችሁ ጥሩ ነገር አድርጋችሁ መሆን አለበት” አላቸው። እነርሱ ጌታ እንደባረካቸው አወቁ። በእርሱ ታምነው አሥራት በመክፈላቸው ተደሰቱ።

ቅዱሳን3፥545