“ቅዱሣን ለሙታን ስለሚደረግ ጥምቀት ተማሩ፣” የትምህርት እና ቃል ኪዳኖች ታሪኮች (2024 [እ.አ.አ])
“ቅዱሣን ለሙታን ስለሚደረግ ጥምቀት ተማሩ፣” የትምህርት እና ቃል ኪዳኖች ታሪኮች
ነሐሴ–ጥቅምት 1840 (እ.አ.አ)
ቅዱሣን ለሙታን ስለሚደረግ ጥምቀት ተማሩ
ላልተጠመቁ የቤተሰብ አባላት ያለ ተስፋ
ጄን ኔይማን በናቩ ትኖር ነበር። ጆሴፍ ስሚዝ ንግግር ወደሚያደርግበት የቀብር ሥነ ሥርዓት ሄደች። የቀብር ሥነ ሥርዓቱ ጄን ስለ ልጇ ሳይረስ እንድታስብ አደረጋት። እርሱም ሞቶ ነበር እንዲሁም አልተጠመቀም። ጄን ስለ ሳይረስ በሀሳብ ጨንቋት ነበር። ከሰማይ አባት ጋር ለመኖር መጠመቅ እንዳለብን ታውቅ ነበር።
ቅዱሳን፣ 1፥421
ጆሴፍ ምን እንደሚሰማት ያውቅ ነበር። ሳይጠመቅ ስለሞተው ወንድሙ አልቪን ተመሳሳይ ነገር ያስጨንቀው ነበር።
ቅዱሳን፣ 1፥421
በቀብር ሥነ ሥርዓቱ ላይ፣ ጆሴፍ እግዚአብሔር ያስተማረውን ነገር አካፈለ። አንድ ሰው ሳይጠመቅ ከሞተ እኛ ለዚያ ሰው መጠመቅ እንችላለን አለ።
ቅዱሳን፣ 1፥421
ጄን ይህን ስትሰማ በጣም ተደሰተች! ከቀብር ሥነ ሥርዓቱ በኋላ፣ ወዲያው ከቤተክርስቲያኗ ሽማግሌ ጋር ወደ ወንዝ ሄደች። እርሱም ለሳይረስ አጠመቃት።
ቅዱሳን፣ 1፥421
ከጥቂት ሳምንታት በኋላ፣ ጆሴፍ ለሙታን ስለመጠመቅ ለቅዱሳን የበለጠ አስተማራቸው። ብዙ የሞቱ ሰዎች መጠመቅ እንደሚፈልጉ ተናገረ። እነርሱ ኢየሱስ ክርስቶስን መከተል ይፈልጋሉ። በሕይወት ያሉ የቤተሰብ አባላት ለእነርሱ እንዲጠመቁ እየጠብቁ እና ተስፋ እያደረጉ ነበር።
ትምህርት እና ቃል ኪዳኖች 128፥15–19፤ ቅዱሳን፣ 1፥423
ቅዱሳኑ ወዲያውኑ ወደ ወንዙ ሮጡ። ለሚወዷቸው ሰዎችም ተጠመቁ። ሃይረም ስሚዝ ለአልቪን ተጠመቀ። በኋላም፣ ጌታ የሙታን ጥምቀት በቤተመቅደስ ውስጥ እንዲደረግ፣ አንድ ሰው የእያንዳንዱን ጥምቀት መዝገብ መያዝ እንዳለበት እና ወንዶች ለወንዶች፣ ሴቶች ደግሞ ለሴቶች እመጠመቅ እንደሚገባቸው አስተማረ።
ትምህርት እና ቃል ኪዳኖች 124፥29–32፤ 127፥5–12፤ 128፥1–9፤ ቅዱሳን፤ 1፥424