በቅዱሳት መጻሕፍት ውስጥ የሚገኙ ታሪኮች
የጥበብ ቃል


“የጥበብ ቃል፣” ትምህርት እና ቃል ኪዳኖች ታሪኮች [2024 (እ.አ.አ)]

“የጥበብ ቃል፣” ትምህርት እና ቃል ኪዳኖች ታሪኮች

የካቲት 1833 (እ.አ.አ)

የጥበብ ቃል

የጌታ የጤና ህግ

የነቢያት ትምህርት ቤት ስብሰባ።

በኑወል እና በአን ውትኒ መጋዘን የላይኛው ወለል ላይ ከእርሱ ጋር እንዲገናኙ ጆሴፍ ስሚዝ ከቤተክርስቲያን ጥቂት ሰዎችን ጋበዘ። በዚያም ወንጌልን እና ሌሎች ጉዳዮችን ተማሩ፣ እንዲሁም በቡድን ሆነው ጸለዩ። ይህንንም ስብሰባ የነቢያት ትምህርት ቤት በማለት ሰየሙት።

ትምህርት እና ቃል ኪዳኖች 88፥117–137Saints [ቅዱሳን]1፥166

ኤማ ስሚዝ ከስብሰባው በኋላ እያጸዳች።

አብዛኞቹ ሰዎች ትምህርቱ በሚሰጥበት ጊዜ ፒፓ ያጨሱ ነበር እና የትምባሆ ቅጠልም ያኝኩ ነበር። ጭሱ አየሩን ደመናማ ያደርገው ነበር፣ እና ትንባሆውም ወለሉን ያቆሽሸው ነበር። ከስብሰባው በኋላ፣ ኤማ ስሚዝ ክፍሉን ለማጽዳት ወደ ፎቁ ወጣች። በጣም ቆሻሻ ነበር።

Saints [ቅዱሳን]1፥167

ኤማ ጆሴፍን ስታነጋግር።

ኤማ ወለሎቹን ደጋግማ ፈተገቻቸው፣ ነገር ግን የትምባሆው ምልክት ሊለቅ አልቻለም። ስለተዝረከረከው ነገር ከጆሴፍ ጋር አወራች።

Saints [ቅዱሳን]1፥167

ጆሴፍ ኤማን ሲያዳምጥ።

ጆሴፍ ኤማን አዳመጠ። እርሷን መስማቱ እግዚአብሔር ስለ ትምባሆው ምን እንደሚሰማው እንዲያስብ አደረገው።

Saints [ቅዱሳን]1፥167

ጆሴፍ መመሪያ ለማግኘት ሲጸልይ።

በመሆኑም ጆሴፍ ጌታን ስለትምባሆው ጠየቀ። ጌታም ለቅዱሳን የጥበብ ቃል እንዳለው ለጆሴፍ ስሚዝ ነገረው።

ትምህርት እና ቃል ኪዳኖች 89፥1–9Saints [ቅዱሳን]1፥167

ጆሴፍና ኤማ እርሱ ስለተቀበለው ራእይ ሲነጋገሩ።

ጌታም ቅዱሳን ማጨስ እንደሌለባቸው፣ ትንባሆ መጠቀም፣ ወይም አልኮል ወይም ‘’ትኩስ መጠጦችን’ ማለትም ቡና እና ሻይ መጠጣት እንደሌለባቸው ተናገረ።

ትምህርት እና ቃል ኪዳኖች 89፥1–9Saints [ቅዱሳን]1፥167

ጆሴፍና ኤማ ከሌሎች ጋር ምግብ ሲጋሩ።

ጌታም ለቅዱሳን ጥራጥሬ እና ፍራፍሬ መልካም ምግቦች እንደሆኑ እንዲሁ አስተማረ። እርሱም በተጨማሪ አንዳንድ ጌዜ ስጋን መብላት እንደሚችሉ ነገራቸው።

ትምህርት እና ቃል ኪዳኖች 89፥10–17Saints [ቅዱሳን]1፥168

ጆሴፍ ስሚዝ በነቢያት ትምህርት ቤት ስብሰባ ላይ የጥበብ ቃልን ሲያካፍል።

ጌታም ለጆሴፍ የጥበብ ቃልን ለመታዘዝ የሚመርጡ ቅዱሳን ጥበቃን እንደሚያገኙ ነገረው። ጌታም በጤና፣ በእውቀት፣ እና በብርታት እንደሚባርካቸው ቃል ገባ። ጆሴፍ በነቢያት ትምህርት ቤት ለነበሩት ሰዎች ስለ ጥበብ ቃል ነገራቸው።

ትምህርት እና ቃል ኪዳኖች 89፥18–21Saints [ቅዱሳን]1፥168

ሰዎች ትምባሆን እና የማጨሻ ፒፓዎቻቸውን ወደ እሳት ውስጥ ሲወረውሩ።

በክፍሉ ውስጥ የነበሩት ሰዎች ትምባሆአቸውን እና ፒፓዎቻቸውን ወደ እሳት ውስጥ ወረወሩ ይህንንም ያደረጉት የጥበብ ቃልን እንደሚያከብሩ ለጌታ ለማሳየት ነበር።

Saints [ቅዱሳን]1፥168