“ናቩን መገንባት፣” የትምህርት እና ቃል ኪዳኖች ታሪኮች (2024 [እ.አ.አ])
“ናቩን መገንባት፣’’ የትምህርት እና ቃል ኪዳኖች ታሪኮች
1840–1842 (እ.አ.አ)
ናቩን መገንባት
ጌታ ለውቧ ከተማ ያለው እቅድ
ጌታ ቅዱሳን በአዲስ ቦታ እንዲሰበሰቡ ነገራቸው። ይህም ሚሲሲፒ በተባለ ትልቅ ወንዝ አጠገብ ነበር። መሬቱ እርጥብ እና ጭቃማ ነበር። ለአንዳንድ ሰዎች ይህ ቦታ ከተማን ለመገንባት ጥሩ ቦታ አይመስልም ነበር። ነገር ግን ነቢዩ ጆሴፍ ስሚዝ በጌታ እርዳታ ውብ ሊያደርጉት እንደሚችሉ ያውቅ ነበር።
ትምህርት እና ቃል ኪዳኖች 124፥25፤ ቅዱሳን፣ 1፥417
ቅዱሳኑ ጥሩ የመኖሪያ ቦታ ለማድረግ ጠንክረው መሥራት ጀመሩ። ነቢዩ ጆሴፍ ከተማዋን ናቩ ብሎ ጠራት፣ ትርጉሙም “ውብ ቦታ” ማለት ነው።
ቅዱሳን፣ 1፥417
ጌታ መንገደኞች መጥተው የሚያርፉበትን ቤት በናቩ እንዲሰሩ ለቅዱሳ ነገራቸው። እርሱ ናቩ ሁሉም ሰው ጥሩ አቀባበል የሚደረግለት ቦታ እንዲሆን ፈለገ።
ትምህርት እና ቃል ኪዳኖች 124፥22–24፣ 60፤ ቅዱሳን፣ 1፥426
ጌታ ለናቩ ታላቅ እቅድ እንዳለው ለነቢዩ ጆሴፍ ነገረው። ቅዱሳኑ ቤተመቅደስ ይገነቡ ዘንድ እዚህ እንዲሰበሰቡ ፈለገ። የእርሱን ቤት ለመገንባት የቻሉትን ያህል እንዲሠሩ ጠየቃቸው። ቅዱሳኑም በፍጥነት መሥራት ጀመሩ።
ትምህርት እና ቃል ኪዳኖች 124፥25–28፣ 44፣ 55፤ ቅዱሳን፣ 1፥420–21፣ 425–27
ጌታ ለቅዱሳን የሚሰጣቸው ታላቅ በረከቶች ስለነበሩት ቤተመቅደስ እንዲሰሩ ፈለገ። በቤተመቅደስ ውስጥ፣ ከጌታ ጋር ቃል ኪዳኖችን ወይም ልዩ ተስፋዎችን ይገባሉ። እንዲሁም የሰማይ አባት ለሁሉም ልጆቹ ስላለው የደስታ እቅድ ይማራሉ።
ትምህርት እና ቃል ኪዳኖች 124፥29–41፤ ቅዱሣን፣ 1፥453–55
ልክ ጌታ እንዳዘዘው ቅዱሳን ቤተመቅደሱን ለመስራት ጠንክረው ሰሩ። ብዙ ጊዜ ወሰደባቸው፣ ነገር ግን እያንዳንዳቸው በቤተመቅደሱ ውስጥ ጌታ ስለሚሰጣቸው ልዩ ተስፋዎች ለሚማሩበት ቀን ጓጉተው ነበር።
ቅዱሳን፣ 1፥453–55።