“ሊብረቲ እስር ቤት፣” የትምህርት እና ቃል ኪዳኖች ታሪኮች [2024 (እ.አ.አ)]
“ሊብረቲ እስር ቤት ፣” የትምህርት እና ቃል ኪዳኖች ታሪኮች
ጥቅምት 1838—መጋቢት 1839 (እ.አ.አ)
ሊብረቲ እስር ቤት
በአስቸጋሪ ጊዜያት ጌታን ማግኘት
በሚዙሪ ይኖሩ የነበሩ ብዙ ሰዎች ቅዱሳንን አይወዷቸውም ነበር። የአገር ገዢም እነርሱን ለማስወጣት ወታደሮችን ላከ። ወታደሮቹ ቅዱሳንን ከየቤታቸው አባረዋቸው፣ ከቤታቸው ውስጥ አንዳንድ ነገሮችን ሰርቀው፣ እና ብዙዎችን ጎድተዋቸው ነበር።
ቅዱሳን፣ 1፥355–56፣ 362፣ 364
ወታደሮች ጆሴፍ ስሚዝን እና ሌሎች የቤተክርስቲያን መሪዎችን አሰሩ።
ቅዱሳን፣ 1፥357–58
ጆሴፍ ምናልባት ከቤተሰቡ ጋር ብቻውን መሆን ይችል እንደሆነ ጠየቀ። ወታደሮቹ አይቻልም አሉ። ጆሴፍን እና ሌሎች እስረኞችን ይዘዋቸው ሄዱ።
ቅዱሳን፣ 1፥366
በአንድ ሌሊት ላይ፣ ጆሴፍ እና ሌሎች እስረኞች ጠባቂዎቹ በቅዱሳን ላይ ስላደረጓቸው መጥፎ ነገሮች እያወሩ ሲስቁ ሰሙ። ጆሴፍ ይህን ከዚህ በላይ ለመስማት ከበደው። ቆመ እናም በቁጣ፣ ‘’ዝምታ!’’ አለ። እርሱ ይናገር የነበረው በእግዚአብሔር ሃይል ነበር። ጠባቂዎቹ ፈሩ። ይቅርታ በማለት ንግግራቸውን አቆሙ።
ቅዱሳን፣ 1፥367–68
በኋላም፣ ጆሰፍ እና ጓደኞቹ ሊብረቲ በሚባል ከተማ ወደነበረው አንድ እስር ቤት ተወሰዱ። እስር ቤቱ ቀዝቃዛ፣ ትንሽ እና ጨለማ ነበር። የሚተኙበት የቆሸሸ የሳር ፍራሽ ብቻ ነበር የነበራቸው። የነበረው ትንሽ ምግብ ብቻ ነበር፣ እርሱንም ለበሽታ ዳርጓቸዋል።
ቅዱሳን፣ 1፥369–70፣ 374፣ 384–85
ጆሴፍ ስለ ቅዱሳን አብዝቶ ተጨነቀ። ወደዳቸው። ስለ እነርሱም ይጨነቅ ነበር። ነገር ግን እነርሱን ለመርዳት ሊያደርግ የሚችለው ነገር አልነበረም።
ቅዱሳን፣ 1፥385–86
ጆሴፍ አብዝቶ ፀለየ። እግዚአብሔር ለምን ቅዱሳንን እንደማይረዳ እና የት እንደነበርም ጠየቀ። እግዚአብሔር እርሱን እና ቤተክርስቲያኗን ረስቶ ይሆንን?
እግዚአብሔር ለጆሴፍ ጸሎት ምላሽ ሰጠ። እንዲህም አለ፣ ‘’ልጄ ሆይ፣ ለነፍስህ ሰላም ይኑርህ።’’ እርሱም ፈተናዎቹ ለዘለዓለም የሚቆዩ እንዳልሆኑ እና ለመልካም እንደሚሆኑለት ለጆሴፍ ነገረው። እግዚአብሔር ለጆሴፍ ኢየሱስ ክርስቶስ እንኳ ከዚህ በከፉ ነገሮች ውስጥ እንዳለፈ እንዲያስታውስ አደረገው። ‘’ለዓለም እና ለዘለዓለም’’ ከጆሴፍ ጋር እንደሚሆን ቃል ገባለት።