‘’ቴሊ ጌታን ታገለግላለች’፣ ’’ የትምህርት እና ቃል ኪዳኖች ታሪኮች [2024 (እ.አ.አ)]
“ቴሊ ጌታን ታገለግላለች፣” የትምህርት እና ቃል ኪዳኖች ታሪኮች
ሚያዝያ 1844–መጋቢት 1852 (እ.አ.አ)
ቴሊ ጌታን ታገለግላለች
ቤተክርስቲያኗን በቱቡዋይ መገንባት
ቴሊ የተባለች ሴት ቱቡዋይ በተባለች በአንዲት ትንሽ ደሴት ውስጥ ትኖር ነበር። የተለያዩ ቤተክርስቲያናት ሚስዮናውያን አንዳንድ ጊዜ ቱቡዋይን ጎብኝተዋታል፣ ነገር ግን አብዛኛውን ጊዜ ብዙ አይቆዩባትም ነበር። በ1844 ዓ.ም (እ.አ.አ)፣ አንድ ቀን ቴሊ ከኋለኛው ቀን ቅዱሳን የኢየሱስ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን ሚስዮናውያን ወደ ቱቡዋይ መምጣታቸውን በሰማች ጊዜ ተደሰተች።
ሚስዮናውያኑ ወደተወሰኑ ትልልቅ ደሴቶች እየሄዱ ነበር። ነገር ግን በቱቡዋይ የነበሩ ህዝቦች እንዲቆዩ እና ወንጌልን እንዲያስተምሩ ፈለጓቸው። ቴሊ እና ባለቤቷ፣ ናቦታ፣ ሚስዮናውያን በቤታቸው መኖር እንደሚችሉ ነገሯቸው። ከሚስዮናውያን አንዱ፣ አዲሰን ፕራት፣ ለዚሁ ተስማማ።
ቅዱሳን፣ 1፥573–74
ቴሊ እና ናቦታ ያሏቸውን ነገሮች ሁሉ ለአዲሰን አካፈሉ። የእነርሱን ቋንቋ እንዲናገርም አስተማሩት። አዲሰን ስለኢየሱስ ክርስቶስ አስተማራቸው።
መንፈስ ቅዱስ የአዳኙ ወንጌል እውነት እንደሆነ ለቴሊ እና ለናቦታ ነገራቸው። እነርሱ በቱቡዋይ የተጠመቁ የመጀመሪያዎቹ ሰዎች ናቸው።
ቅዱሳን፣ 1፥573–74
ቴሊ፣ ናቦታ እና አዲሰን የልብ ጓደኞች ሆኑ። አብረው ይጓዙ ነበር እናም በቱቡዋይ እና ሌሎች ደሴቶች ወንጌልን አስተማሩ። በቱቡዋይ ያሉ ሰዎች ለቅዱሳን በቤተክርስቲያኗ ባይቀላቀሉ ይሻል ነበር በሚሏቸው ጊዜ፣ ቴሊ ከቅዱሳት መጻህፍት እየጠቀሰች ቤተክርስቲያኗ እውነት እንደሆነች ታስተምር ነበር።
ቅዱሳን፣ 2፥27፣ 45
ብዙ ሰዎች በቱቡዋይ ወንጌልን እንዲማሩ ቴሊ ለመርዳት ትፈልግ ነበር። ምሽት በሆነ ጊዜ የቅዱሳት መጻህፍት ጥቅሶችን ወደ መዝሙር በመቀየር ብዛት ያላቸው ሰዎች ከእርስዋ ጋር እንዲዘምሩ ትጋብዝ ነበር። የቴሊን መዝሙሮች መዘመር ለብዙ ሰዎች ቅዱሳት መጻህፍትን እንዲማሩ እና የተማሩትን እንዲያስታውሱ ረድቷቸዋል።
ከዓመታት በኋላ፣ የአዲሰንን ቤተሰብ ጨምሮ፣ ብዙ ሚስዮናውያን ወደ ቱቡዋይ መጡ። ቴሊ በቤቷ ተቀበለቻቸው። እርስዋ የቱቡዋይ ሴቶችን ለማገልገል፣ ከአዲሰን ባለቤት፣ ከሉዊዛ ጋር ሰራች።
ቅዱሳን፣ 2፥133–34
ከጊዜ በኋላ፣ ሚስዮናውያን ቱቡዋይን እና ሌሎች ደሴቶችን ለቀው እንዲወጡ ተገደዱ። ነገር ግን ቴሊ ቅዱሳንን ማስተማሯን እና መምራቷን ቀጠለች። በቴሊ ምሳሌነት እና አገልግሎት ምክንያት፣ ቤተክርስቲያኗ በቱቡዋይ ጠንካራ ሆና ቀጥላለች።
ቅዱሳን፣ 2፥150–51