በቅዱሳት መጻሕፍት ውስጥ የሚገኙ ታሪኮች
የፈውስ ቀን


“የፈውስ ቀን፣” የትምህርት እና ቃል ኪዳኖች ታሪኮች [2024 (እ.አ.አ)]

“የፈውስ ቀን፣” የትምህርት እና ቃል ኪዳኖች ታሪኮች

ሚያዝያ–ሐምሌ 1839 (እ.አ.አ)

የፈውስ ቀን

በእግዚአብሔር ሃይል ህሙማንን መባረክ

የእስር ቤቱ ጠባቂ ጆሴፍ ስሚዝን ሲያናግረው።

ጆሴፍ ስሚዝ እና ሌሎች የቤተክርስቲያን መሪዎች በምዙሪ ታስረው እያለ፣ አንዳንድ ጠባቂዎች ወደ ሌላ እስር ቤት ወሰዷቸው። ጠባቂዎቹ ለእስረኞቹ ደጎች ነበሩ። አንድ ሌሊት፣ የጠባቂዎቹ መሪ ሊተኛ እንደሆነ፣ እና ጆሴፍ እና ጓደኞቹ አምልጠው ቢሄዱ ሊያቆማቸው እንደማይችል ለጆሴፍ ነገረው።

Saints [ቅዱሳን]1፥392–93

ጆሴፍ ቤተሰቡን ሰላም ሲል።

ጆሴፍ እና ሌሎች የቤተክርስቲያን መሪዎች አመለጡ። ቤተሰቦቻቸው ክውንሲ በሚባል ከተማ ውስጥ እየኖሩ አገኟቸው።

Saints [ቅዱሳን]1፥395–96

ሰዎች ለቅዱሳን ምግብ እና መጠለያ ሲሰጡ።

በክውንሲ ያሉ ሰዎች ለቅዱሳን ደጎች ነበሩ። ለቅዱሳን ምግብ እና ልብስ እናም መጠለያ ሰጧቸው።

Saints [ቅዱሳን]1፥377

ቅዱሳን ናቩን መገንባት ጀምረዋል።

ቅዱሳን በክውንሲ ያሉ ህዝቦች ላሳዩት ደግነት ምስጋናን አቅርበዋል። ነገር ግን ጆሴፍ የራሳቸው የሆነ የመኖሪያ ስፍራ እንደሚያስፈልጋቸው አውቋል። የቤተክርስቲያኗ መሪዎች ሌላ ማንም ሰው የማይፈልገውን የተወሰነ መሬት ገዙ፣ እና ቅዱሳንም ወደዚያ ተዛወሩ።

Saints [ቅዱሳን]1፥399–400

አንዲት ሴት በወባ የተያዘችን ሌላ ሴት ስትንከባከብ።

መሬቱም በአንድ ትልቅ ወንዝ አጠገብ ነበር። እርጥበታማ እና ጭቃማ እና ትንኝ የሞላበት ነበር። ትንኞቹ አብዛኞቹን ቅዱሳን ወባ በተባለ በሽታ በጣም በሽተኛ አድርገዋቸው ነበር። አንዳንዶቹ ሞቱ።

Saints [ቅዱሳን]1፥402

ጆሴፍ ስሚዝ እና ውልፈርድ ውድረፍ ለአንድ ህመምተኛ ወጣት የክህነት በረከትን እየሰጡ።

ጆሴፍ ብዙ ሰዎች እንደታመሙ ባየ ጊዜ፣ አንዳንድ የቤተክርስቲያኗ መሪዎችን ሰበሰበ እና ከእርሱ ጋር እንዲመጡ ጠየቀ። በጠዋቱ ጊዜ በሙሉ፣ ከቤተሰብ ወደ ቤተሰብ፣ ህመምተኞችን ሲጎበኙ እና ሰባርኩ ዋሉ። ህመማቸውንም ለመፈወስ የኢየሱስ ክርስቶስን ሃይል ተጠቀሙ።

Saints [ቅዱሳን]1፥402

ጆሴፍ ከኢላይጃ ፎርድሃም ጋር ሲነጋገር።

አንድ የጎበኙት ሰው ኢላይጃ ፎርድሃም ይባል ነበር። በጣም ታሞ ነበር፣ ባለቤቱም በቅርቡ የሚሞት መስሏት ነበር። ጆሴፍ ኢላይጃን እንዲፈወስ እምነት እንዳለው ጠየቀው።

Saints [ቅዱሳን]1፥402

ኢላይጃ እንደሚፈወስ እምነት ያለው መሆኑን ለጆሴፍ ሲነግረው።

ኢላይጃም፣ ‘’በጣም የረፈደ ነው ብዬ ፈርቻለሁ።’’ ጆሴፍ ኢላይጃን በኢየሱስ ክርስቶስ ያምን እንደሆነ ጠየቀው። ‘’አምናለሁ፣ ወንድም ጆሴፍ፣’’ በማለት መለሰለት።

Saints [ቅዱሳን]1፥402

ኢላይጃ የክህነት በረከትን ከተቀበለ በኋላ ቆመ።

ጆሴፍም እርሱን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ባረከው። ኢላይጃ ተነሳ። ኢየሱስም ፈወሰው! ኢላይጃ ጆሴፍን እስከሚቀጥለው ቤት ድረስ ተከተለው እና ሌሎች ሰዎችን በመባረክም ረዳው።

Saints [ቅዱሳን]1፥402–3