“ናቩን ለቅቆ ወደ ምእራብ መሄድ፣” የትምህርት እና ቃል ኪዳኖች ታሪኮች [2024 (እ.አ.አ)]
“ናቩን ለቅቆ ወደ ምእራብ መሄድ፣” የትምህርት እና ቃል ኪዳኖች ታሪኮች
ሰኔ 1844–ሐምሌ 1847 (እ.አ.አ)
ናቩን ለቅቆ ወደ ምእራብ መሄድ
ቅዱሳን ለጌታ ቃል ይገባሉ እና የገቡትንም ቃል ይጠብቃሉ
ጆሴፍ ስሚዝ ሞተ። አሁን ብሪገም ያንግ እና ሌሎች ሐዋርያት ቤተክርስቲያኗን ይመሩ ነበር። ብሪገም ያንግ ቅዱሳን ከዚህ በኋላ በናቩ ውስጥ ደህንነት እንደማይሰማቸው አውቀው ነበር። መሄድ ነበረባቸው። ነገር ግን በመጀመሪያ፣ ጌታ የቤተመቅደሱን ግንባታ እንዲያጠናቅቁ ፈልጓል። እነርሱ ከእርሱ ጋር ቃል ኪዳን እንዲገቡ እና እንደቤተሰብ እንዲተሳሰሩ ፈልጓል።
ቅዱሳን፣ 1፥571፣ 579–80
ከጥቂት ወራት በኋላ፣ ሰዎች በዚያ ቃል ኪዳንን እንዲያደርጉ ቤተመቅደሱ ዝግጁ ሆነ። በሺዎች የሚቆጠሩ ቅዱሳን ወደ ቤተመቅደሱ መጡ። ከጌታ ጋር ቃል ኪዳን እንዲያገቡ ለመርዳት ብሪገም እስከ እኩለ ሌሊት ድረስ በቤተመቅደስ ውስጥ ቆይተው ነበር። በመጨረሻም፣ እያንዳንዱ ሰው ናቩን ለቅቆ መሄድ እንዳለበት ብሪገም ተናገሩ።
ቅዱሳን፣ 1፥582
ብሪገም በሚቀጥለው ጠዋት ሲነቁ፣ የበለጠ ቁጥር ያላቸው ቅዱሳን በቤተመቅደስ እየተጠባበቁ ነበር። ብሪገም እነርሱ በናቩ መቆየታቸው መልካም እንዳልሆነ ነገራቸው። በምእራብ ውስጥ አዲስ ቤት መፈለግ ነበረባቸው። እዚያም በደረሱ ጊዜ አዲስ ቤተመቅደስ መስራት እንደሚችሉ ቃል ገቡላቸው።
ቅዱሳን፣ 1፥582–83፣ 2፥13–14
ነገር ግን ቅዱሳኑ ከዚያ አልሄዱም። ወደ አዲሱ ቤታቸው ለመሄድ ጉዞ ከመጀመራቸው በፊት ከጌታ ጋር ቃል ኪዳንን ማድረግ ፈልገዋል።
ቅዱሳን፣ 1፥583
ብሪገም ፊቶቻቸውን ተመለከቱ እናም ሃሳባቸውን ቀየሩ። ቀሪውን የቀኑን ጊዜ አሳለፈው እናም በሚቀጥለው ቀን፣ ቅዱሳን በቤተመቅደስ ቃል ኪዳን ለማድረግ እንዲችሉ ረዷቸው።
ቅዱሳን፣ 1፥583
አሁን ቅዱሳን ከጌታ ጋር ቃል ኪዳንን ገብተዋል፣ ናቩን የመልቀቅ ጊዜ አሁን ነበር። ጌታ ለእነርሱ ስፍራን እንዳዘጋጀላቸው ብሪገም አውቀዋል። ይህንንም በራእይ ተመልክተዋል። እነርሱም ጉዞአቸውን ጀመሩ። የአየሩ ሁኔታ ቀዝቃዛ ነበር፣ እና መሬቱም ጭቃማ ነበር። ህዝቡም ታመሙ። በዚህ ጊዜ ምግብ አልቆባቸው ነበር።
ቅዱሳን፣ 2፥16–18፣ 20–21
ቅዱሳን ገና ረዥም መንገድ ይቀራቸው ነበር። ብሪገም ይህ አይነቱን ረዥም እና ከባድ ጉዞ እንዴት ማድረግ እንደሚችሉ በማሰብ ግራ ተጋቡ። ከእግዚአብሔር እርዳታን በመፈለግ ጸለዩ።
ቅዱሳን፣ 2፥46
ጌታ ለብሪገም ራእይን ሰጣቸው። ቅዱሳንን እንዴት መምራት እንዳለባቸው ለብሪገም አስተማረ። እርሱም እርስ በርሳቸው ተረዳዱ እና ድሆችንም ደግፉ አሉ።
ጌታም ቅዱሳን ከእርሱ ጋር የገቡትን ቃል ኪዳን ማስታወስ እንዳለባቸው ተናገረ። ይህንንም ቢያደርጉ፣ እንደሚባርካቸው እና በመንገዳቸው ሁሉ እንደሚረዳቸው ተናገረ።
ትምህርት እና ቃል ኪዳኖች 136፥4፣ 11፣ 42፤ ቅዱሳን፣ 2፥47
አሁንም ጉዞው በጣም ከባድ ነበር። አንዳንድ ሰዎችም ሞቱ። ነገር ግን በቤተመቅደሱ ቃል ኪዳናቸው ምክንያት፣ ቅዱሳን የቤተሰብ አባሎቻችውን ዳግም እንደሚያገኟቸው አውቀዋል።
ከጥቂት ወራት በኋላ፣ የመጀመሪያዎቹ ቅዱሳን በ1847 (እ.አ.አ) ወደሶልት ሌክ ሸለቆ ደርሰዋል። ብሪገም ያንግ ሸለቆውንም እንዳዩ “ይህ ትክክለኛው ቦታ ነው” በማለት ተናገሩ። በራእይ ከተመለከቱት ጋር ተመሳሳይ ስፍራ ነበር። ይህ ቅዱሳን ደህንነት የሚሰማቸው ስፍራ ነበር። በዚህ ጌታን ሊያመልኩት እና ስራውንም በሰላም ሊሰሩ ይችላሉ።
ቅዱሳን፣ 2፥17፣ 64–67
በዓመታት መካከል፣፣ ብዙ ቅዱሳን ወደዚህ ደርሰዋል። እነርሱም ሰዎች ከጌታ ጋር ቃል ኪዳን የሚገቡባቸውን ሌሎች ብዙ ቤተመቅደሶችንም ገንብተዋል። የኢየሱስ ክርስቶስን ወንጌል ለማስተማር በዓለም ዙሪያ ሚስዮናውያንን ልከዋል። በየስፍራው የሰማይ አባት ልጆችን እየባረከች፣ የአዳኙ ቤተክርስቲያን ማደጓን ቀጥላለች።