በቅዱሳት መጻሕፍት ውስጥ የሚገኙ ታሪኮች
የዴዚዴሪያ ህልም


“የዴዚዴሪያ ህልም፣” የትምህርት እና ቃል ኪዳኖች ታሪኮች [2024 (እ.አ.አ)]

“የዴዚዴሪያ ህልም፣” የትምህርት እና ቃል ኪዳኖች ታሪኮች

1880–1886 (እ.አ.አ)

የዴዚዴሪያ ህልም

በሜክሲኮ ውስጥ በጌታ መመራት

ዴዚዴሪያ ያኔዝ ህልም እያየች።

ዴዚዴሪያ በናፓላ፣ ሜክሲኮ ውስጥ ትኖር ነበር። በአንድ ሌሊት፣ ዴዚዴሪያ በሜክሲኮ ከተማ ውስጥ እየተሰራ ስላለ አንድ ትንሽ መጽሐፍ ህልም አየች። እርሱም ይሰኝ የነበረው Voz de amonestación፣ ወይም የማስጠንቀቂያ ድምጽ ነበር። ዴዚዴሪያ በነቃች ጊዜ፣ ያንን መጽሐፍ ማግኘት እንደነበረባት አወቀች።

ቅዱሳን2፥477

ዴዚዴሪያ ስለህልሙ ለልጇ ነገረችው።

ነገር ግን የሜክሲኮ ከተማ ሩቅ ስለነበር የዚህ አይነቱን ረዥም ጉዞ ለማድረግ የዴዚዴሪያ እድሜ በጣም የገፋ ነበር። እርስዋም ያንን መጽሐፍ ፈልጋ እንድታገኝ ጌታ የሚፈልግ መሆኑ ተሰማት። በመሆኑም ለልጇ፣ ለሆሴ፣ ስለህልሙ ነገረችው። መጽሀፉ አስፈላጊ የነበረ መሆኑንም ጭምር አመነች። እርሱም ፈልጎ እንደሚያገኝላት ለእናቱ ነገራት።

ቅዱሳን2፥478

ሆሴ ሜክሲኮ ከተማ ሲደርስ።

ሆሴ በሜክሲኮ ከተማ በደረሰ ጊዜ፣ መንገዶቹ የተጨናነቁ፣ ድምጽ የበዛባቸው እና በህዝብ የተሞሉ ነበሩ። እንደዚህ ባለ በህዝብ በተጨናነቀ ስፍራ ውስጥ መጽሐፉን እንዴት ሊያገኝ ይችላል?

ቅዱሳን2፥478

ሆሴ ጄምስ ስቲዋርድን ሲያገኘው።

ከጥቂት ቀናት በኋላ፣ ሆሴ ጄምስ ስቲዋርት የተባለን ሚስዮናዊ አገኘ። ጄምስ አንድን መጽሐፍ ለማሳተም በመስራት ላይ እንደሆነ እና መጽሐፉም Voz de amonestación [የማስጠንቀቂያ ድምጽ] እንደሚሰኝ ተናገረ።

ቅዱሳን2፥478

ጄምስ ስለ መፅሐፈ ሞርሞን እየተናገረ።

ሆሴ በጣም ተደስቶ ነበር! ስለ እናቱ ህልም ለጄምስ ነገረው። ጄምስም ሚስዮናውያን Voz de amonestación [የማስጠንቀቂያ ድምጽ]ን በመጠቀም ስለኢየሱስ ክርስቶስ እና መፅሐፈ ሞርሞን ስለተባለው አዲስ ቅዱስ መጽሐፍ ለህዝቡ ለማስተማር እንደሚችሉ ገለጸለት።

ቅዱሳን2፥478

ስለ ወንጌል ለመማር ይረዳው ዘንድ ጄምስ መጽሐፎቹን ለሆሴ ሲሰጠው።

Voz de amonestación [የማስጠንቀቂያ ድምጽ] እስካሁን አላለቀም ነበር፣ እናም መፅሐፈ ሞርሞንም ወደ ስፓኒኛ ቋንቋ አልተተረጎመም ነበር። ነገር ግን እርሱን እና እናቱን ስለኢየሱስ ክርስቶስ፣ ስለመፅሐፈ ሞርሞን፣ እና ዳግም ስለተመለሰችው ቤተክርስቲያን ለመማር እንዲረዳቸው፣ ጄምስ ለሆሴ ሌሎች መጽሀፍትን እና ወረቀቶችን ሰጠው።

ትምህርት እና ቃል ኪዳኖች 90፥11ቅዱሳን2፥478–79

ሆሴ እና እናቱ በአንድነት ስለወንጌል እየተማሩ።

ሆሴ እናቱን ለማግኘት ወደ ቤቱ በፍጥነት ሄደ። አብረውም ወንጌልን አጠኑ፣ እና እውነት እንደነበር አወቁ። ዴዚዴሪያ ሚስዮናውያን መጥተው እንዲያጠምቋት ጠየቀች።

ቅዱሳን2፥479

ዴዚዴሪያ፣ ሆሴ፣ እና የሆሴ ሴት ልጅ፣ ካርሜን እየተጠመቁ።

ዴዚዴሪያ በሜክሲኮ ውስጥ በመጀመሪያ ከተጠመቁት ሴቶች እንዷ ነበረች። ሆሴ እና ሴት ልጁም እንዲሁ ተጠምቀዋል።

ቅዱሳን2፥479

ዴዚዴሪያ የመጽሐፈ ሞርሞንን አንድ ቅጂ እየተቀበለች።

Voz de amonestación [የማስጠንቀቂያ ድምጽ] መታተሙ ሲፈጸምም፣ ሆሴ በኖፓላ ከሌሎች ጋር ለመካፈል አስር ቅጂዎችን ለእናቱ ለመስጠት አገኘ። ከዓመታት በኋላ፣ መፅሐፈ ሞርሞን በመጨረሻ በስፓኒኛ ቋንቋ ሲታተም፣ ዴዚዴሪያ በሜክሲኮ ውስጥ ይህንን ለማግኘት የመጀመሪያዋ ግለሰብ ነበረች። እርስዋም ጌታ ዳግም ወደተመለሰው ቤተክርስቲያኑ እንደመራት አውቃለች።

ትምህርት እና ቃል ኪዳኖች 88፥81ቅዱሳን2፥479