“ሲድኒ እና ፊቢ ሪግደን፣” የትምህርት እና ቃል ኪዳኖች ታሪኮች [2024 (እ.አ.አ)]
“ሲድኒ እና ፊቢ ሪግደን፣” የትምህርት እና ቃል ኪዳኖች ታሪኮች
ጥቅምት–ህዳር 1830 (እ.አ.አ)
ሲድኒ እና ፊቢ ሪግደን
ወንጌልን ለመቀበል ሕይወታቸውን መለወጥ
ፓርሊ ፕራት እና ሌሎች ለጥንታዊ አሜሪካውያን ወንጌልን ሊያካፍሉ እየሄዱ ነበር። በመንገዳቸው ላይ፣ ፓርሊ ጓደኛውን ስድኒ ሪግደንን ለመጎብኘት ቆም ለማለት ፈለገ። ሲድኒ ከመጽሐፍ ቅዱስ ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ ለፓርሊ ያስተማረው ሰባኪ ነበር። አሁን ፓርሊ ሲድኒን ከመፅሐፈ ሞርሞን ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ ሊያስተምረው ፈለገ።
ትምህርት እና ቃል ኪዳኖች 32፤ ቅዱሳን፣ 1–99
ፓርሊ፣ ስለመጽሐፈ ሞርሞን ለሲድኒ ነገረው እንዲሁም እንዲያነበው ጋበዘው። ሲድኒ እርግጠኛ አልነበረም፣ ሆኖም ፓርሊ ጓደኛው ስለነበረ እንደሚያነበው ቃል ገባ።
ቅዱሳን፣ 1፥100
ሲዲኒ መፅሐፈ ሞርሞንን ባነበበው ጊዜ ከእግዚአብሔር የመጣ እንደሆነ አመነ። ስሜቱን ለሚስቱ ለፊቢ አካፈለ።
ቅዱሳን፣ 1፥101
ሆኖም ሲድኒ ቀጥሎ ምን ማድረግ እንደነበረበት እርግጠኛ አልነበረም። ከተጠመቀ በእርሡ ቤተክርስቲያን ውስጥ ያለውን የሰባኪነት ስራውን ያጣል። ፊቢን እና ስድስት ልጆቻቸውን እንዴት መንከባከብ ይችላል? በእርሡ ቤተክርስቲያን ውስጥ ያሉ ሰዎች ምን ይሰማቸዋል? እርዳታ ለማግኘት ወደ ሰማይ አባት ጸለየ፣ ከዚያም ሠላማዊ ሥሜት ተሠማው።
ቅዱሳን፣ 1:101፤ ትምህርት እና ቃል ኪዳኖች 19፥23
ሲድኒ፣ የተደላደለ ኑሯቸውን ለመተው እና ይህን አዲስ ቤተክርስቲያን ከእርሱ ጋር ለመቀላቀል ፈቃደኛ ስለመሆኗ ፊቢን ጠየቃት። “የእኔ ፍላጎት የእግዚአብሔርን ፈቃድ ማድረግ ነው፣ ሞት ወይም ሽረት ቢሆንም” አለች። ለመጠመቅ ወሠኑ።
ቅዱሳን፣ 1፥101
በኋላም፣ ሲድኒ ከነቢዩ ጆሴፍ ስሚዝ ጋር ተገናኘ። ጌታ በጆሴፍ በኩል ለሲድኒ መልዕክት ሰጠው። ሲድኒ ያደረጋቸውን መልካም ነገሮች እንደተመለከተ እና ጸሎቱንም እንደሰማው ተናገረ። ጌታ፣ እርሡ የሚሠራው ታላቅ ሥራ እንዳለው ለሲድኒ ነገረው። ሲድኒ ታላላቅ ነገሮችን ያደርጋል።