በቅዱሳት መጻሕፍት ውስጥ የሚገኙ ታሪኮች
በምዙሪ ውስጥ የነበር ችግር


“በምዙሪ ውስጥ የነበረ ችግር፣” የትምህርት እና ቃል ኪዳኖች ታሪኮች [2024 (እ.አ.አ)]

“በምዙሪ ውስጥ የነበረ ችግር፣” የትምህርት እና ቃል ኪዳኖች ታሪኮች

ሐምሌ 1831–ሐምሌ 1833 (እ.አ.አ)

በምዙሪ ውስጥ የነበር ችግር

በአደገኛ ጊዜያት እምነትን አጠንክሮ መያዝ

በኢንዲፔንደንስ የነበሩ አንዳንድ ሰዎች ወደዚያ እየገቡ ባሉ ቅዱሳን እየተበሳጩ።

ብዙዎቹ ቅዱሳን በኢንዲፔንደንስ፣ ምዙሪ ለመኖር መጥተዋል። ጌታ በዚያ የጽዮንን ከተማ እንዲገነቡ ፈልጓል። ነገር ግን በኢንዲፔንደንስ እየኖሩ የነበሩ ቅዱሳን እና በዚያ የነበሩት ህዝቦች አልተስማሙም። በብዙ ነገሮች አይስማሙም ነበር። በከተማው የነበሩ አንዳንድ ሰዎች ብስጩዎች ነበሩ እና ቅዱሳኑ እንዲወጡላቸው ይፈልጉ ነበር።

ትምህርት እና ቃል ኪዳኖች 57፥1–3Saints [ቅዱሣን]1፥171–74

በኢንዲፔንደንስ የነበሩ መሪዎች ከኤድዋርድ ፓርትሪጅ ጋር ሲገናኙ።

ኤድዋርድ ፓርትሪጅ በኢንዲፔንደንስ ኤጲስ ቆጶስ ነበር። ከከተማው መሪዎች ጋር ለስብሰባ መጣ። እነርሱም ቅዱሳኑ ከኢንዲፔንደንስ ለቀው መውጣት አለባቸው አሉ። ኤጲስ ቆጶስ ፓትሪጅ እግዚአብሔር ቅዱሳንን በኢንዲፔንደንስ ጽዮንን እንዲገነቡ እንደሚፈልግ ያውቅ ነበር። ቅዱሳኑ ለቀው መውጣት አይችሉም አለ።

Saints [ቅዱሳን]1፥176

ቁጡ ሰዎች ቤቶችን እና ህንጻዎችን እያፈራረሱ።

ቁጡ ሰዎች ቅዱሳን የገነቧቸውን ቤቶች እና ህንጻዎችን ማፈራረስ ጀመሩ።

Saints [ቅዱሳን]1፥177–78182

ሰዎች ኤድዋርድ ፓርትሪጅን እና ቻርልስ አለንን ሲይዟቸው።

ሰዎቹ ኤጲስ ቆጶስ ፓርትሪጅን እና ሌላኛውን ሰው ቻርልስ አለንን ከቤታቸው ወሰዷቸው። ሁለቱን ሰዎች ወደ ከተማው መካከል ጎተቷቸው።

Saints [ቅዱሳን]1፥179

ኤድዋርድ እና ቻርልስ በሬንጅ እና በላባ ሲሸፈኑ።

ኤጲስ ቆጶስ ፓርትሪጅ፣ ‘’ለሃይማኖቴ መሰቃየት ካለብኝ፣ ከእኔ በፊት የነበሩት ሌሎች ከደረሰባቸው በላይ አይሆንም’’ በማለት ተናገረ። ሰዎቹ ኤጲስ ቆጶስ ፓርትሪጅን እና ቻርልስን ወደምድር ገፈተሯቸው። የፈላ ሬንጅ እና ላባዎችን በመላ በአካላቸው ላይ አደረጉ።

Saints [ቅዱሳን]1፥179–80

ውልያም መክለለን በቁጥቋጦው ውስጥ ተደብቋል።

በኢንዲፔንደንስ የቤተክርስቲያን አባል የነበረው ውልያም መክለለን ቁጡዎቹ ሰዎች ያደርጉ ስለነበረው ነገር ሰማ። እርሱ በጣም ፈራ እና ለመደበቅ ወደ ቁጥቋጦው ውስጥ ሮጠ።

Saints [ቅዱሳን]1፥182

ውልያም ቢያዝ ምን ማድረግ እንዳለበት እያሰበ።

ውልያም ብስጩዎቹ ሰዎች ቢያገኙት ምን ሊፈጠር እንደሚችል አሰበ። በእርሱ ምክንያት ሊገሉት እንኳ ቢፈልጉ፣ አሁንም መጽሐፈ ሞርሞን እውነት ነው በማለት ይናገራልን?

Saints [ቅዱሳን]1፥182–83

ኦሊቨር ካውድሪ እና ዴቪድ ዊትመር ውልያምን ሲያገኙት።

የውልያም ጓደኞች ኦሊቨር ካውድሪ እና ዴቪድ ዊትመር በቁጥቋጦዎቹ ውስጥ አገኙት። ኦሊቨር እና ዴቪድ በመጽሐፈ ሞርሞን እንዳመኑ ውልያም ያውቅ ነበር። መልአክ የወርቅ ሰሌዳዎቹን አሳይቷቸዋል። ‘’ንገሩኝ፣’’ በማለት ውልያም ጠየቃቸው፣ ‘’ያ መጽሐፈ ሞርሞን እውነት ነውን?’’

Saints [ቅዱሳን]1፥183

ኦሊቨር እና ዴቪድ ለውልያም ምስክርነታቸውን ሲያካፍሉ።

ኦሊቨር እና ዴቪድ መጽሐፈ ሞርሞን እውነት እንደሆነ ለውልያም ነገሩት። የተበሳጩት ሰዎች ሊገድሏቸው ቢፈልጉም እንኳ፣ ለህዝቡ ምስክርነታቸውን ማካፈላቸውን በፍጹም እንደማያቆሙ ተናገሩ። ‘’አምናችኋለሁ፣’’ በማለት ውልያም ተናገረ።

ትምህርት እና ቃል ኪዳኖች 17፥3–6Saints [ቅዱሳን]1፥183