Scripture Stories
ነቢዩ ሙሴ


“ነቢዩ ሙሴ፣” የብሉይ ኪዳን ታሪኮች [2022 (እ.አ.አ)]

“ነቢዩ ሙሴ፣” የብሉይ ኪዳን ታሪኮች

ዘፀአት 2–3

ነቢዩ ሙሴ

የጌታን ህዝብ ነጻ ለማውጣት የተጠራ

ምስል
ግብፃዊው እስራኤላዊውን ሲደበድብ

ሙሴ ያደገው እንደ ፈርዖን ሴት ልጅ ወንድ ልጅ ነበር። ሙሴ ግብፃውያን በእስራኤላውያን ላይ ጨካኝ እንደሆኑ አየ። ግብፃውያኑ እስራኤላውያንን ባሪያቸው በማድረጋቸው አዝኖ ነበር።

ዘጸአት 2፥10–11

ምስል
ሙሴ እስራኤላውያንን ሲከላከል

አንድ ቀን ሙሴ አንድ ግብፃዊ አንድን እስራኤላዊ ሲመታ አየ። እስራኤላዊውን ለመከላከል ሙሴ ግብፃዊውን ገደለው።

ዘጸአት 2፥11–14

ምስል
ሙሴ በምድረበዳ ውስጥ

ፈርዖን ይህንን ሲያውቅ፣ ሙሴን ለመግደል ፈለገ፤ ነገር ግን ሙሴ ከግብፅ ሸሸ።

ዘፀአት 2፥15

ምስል
ሙሴ እና ቤተሰብ

ሙሴ ምድያም ወደምትባል ስፍራ መጣ፣ በዚያም ሲፎራ የተባለች ሴት አገኘ። ተጋቡና ልጆችን ወለዱ።

ዘጸአት 2፥21–22

ምስል
ሙሴ የሚቃጠል ቁጥቋጦን እየተመለከተ

ሙሴ በምድያም ውስጥ በነበረበት ጊዜ እየነደደ የነበረን ቁጥቋጦ አየ፣ እሳቱ ግን ቁጥቋጦውን አላቃጠለውም። ጌታ በእሳት ውስጥ ተገልጦ ሙሴን አነጋገረው።

ዘጸአት 3፥1–6

ምስል
ኢየሱስ ከሙሴ ጋር ሲነጋገር

ጌታ እስራኤላውያን በግብፅ እየተሰቃዩ እንደሆኑ አውቃለሁ አለ። ወደ ግብፅ እንዲመለስና እስራኤላውያንን በነጻነት እንዲለቅ ለፈርዖን እንዲነግረው ሙሴን አዘዘው። ጌታ ሙሴ እስራኤላውያንን ነፃ እንዲያወጣ እና ወደ ተስፋይቱ ምድር እንዲወስድ እረዳዋለሁ አለ።

ዘጸአት 3፥7–18