Scripture Stories
አብርሐም እና ይስሀቅ


“አብርሐም እና ይስሀቅ፣” የብሉይ ኪዳን ታሪኮች [2022 (እ.አ.አ)]

“አብርሐም እና ይስሀቅ፣” የብሉይ ኪዳን ታሪኮች

ዘፍጥረት 17፤ 21–22

አብርሐም እና ይስሀቅ

አባት፣ ልጅ፣ እና መስዋዕት

ምስል
አብርሐም፣ ሣራ፣ እና ህጻኑ

አብርሐም እና ሣራ፣ ልክ ጌታ ቃል እንደገባው፣ ወንድ ልጅ ወለዱ። ስሙንም ይስሀቅ ብለው ሰየሙት።

ዘፍጥረት 17፥921፥1–3

ምስል
አብርሐም ይስሀቅን ሲያስተምር

ይስሀቅን ይወዱት ነበር። ትክክለኛውን እንዲመርጥ እና በጌታ እንዲታመን አስተምረውትም ነበር።

ዘፍጥረት 21፥8

ምስል
አብርሐም እና ሣራ ይስሀቅን ሲመለከቱ

በይስሐቅ በኩል መላ ምድርን ለመባረክ እንደሚያድጉ ጌታ ለአብርሃምና ለሣራ ቃል ገባላቸው። ነገር ግን አንድ ቀን ይስሀቅን ወደ ሞሪያ ተራራ እንዲወስድና ይስሀቅን እንደ መሥዋዕት እንዲያቀርብ ጌታ ለአብርሐም ነገረው።

ዘፍጥረት 17፥1–822፥1–2

ምስል
አብርሐም እና ይስሀቅ እየተጓዙ

ወደ ተራራው እየተጓዙ ሳሉ፣ ይስሐቅ የመሥዋዕቱ በግ የት እንዳለ ጠየቀ። አብርሐምም ጌታ ይሰጠናል ብሎ መለሰለት።

ዘፍጥረት 22፥4–8

ምስል
አብርሐም እና ይስሀቅ መሰዊያ ሲገነቡ

በምሪያ ተራራ ላይ፣ አብርሐም መሰዊያ ገንብቶ በላዩ ላይ እንጨት አኖረ።

ዘፍጥረት 22፥8–9

ምስል
አብርሐም ይስሀቅን ሊሰዋ ሲዘጋጅ

እግዚአብሔር እንዳዘዘውም፣ አብርሐም ይስሐቅን በመሠዊያው ላይ እንዲተኛ ጠየቀው። ልክ አዳኙ ኢየሱስ ክርስቶስ በአባቱ እንደታመነ፣ ይስሀቅም አብርሃምን አመነ።

ዘፍጥረት 22፥9

ምስል
መልዓክ ለአብርሐም እና ለይስሀቅ ሲገለጥ

አብርሐም ይስሀቅን ሊሠዋ ሲል፣ የጌታ መልአክ አቆመው። አብርሐም በጌታ ያለውን እምነት አሳየ። አብርሐም ሁልጊዜ ጌታን እንደሚከተል ያውቅ ነበር።

ዘፍጥረት 19፥10–12

ምስል
አውራ በግ በቁጥቋጦች ውስጥ ተይዞ

አብርሐም ቀና ብሎ ተመለከትና አንድ አውራ በግ በቁጥቋጦች ውስጥ ተይዞ ተመለከተ። ጌታ ለመሥዋዕት አውራ በግ አቀረበ።

ዘፍጥረት 22፥13

ምስል
አብርሐም እና ይስሀቅ ወደሰማይ ሲመለከቱ

የሰማይ አባት ልጁን ኢየሱስ ክርስቶስን እንደ መስዋዕት እንዴት እንደሚያቀርብ አብርሐም እና ይስሀቅ ተማሩ። ታዛዥ በመሆኑ ምክንያት ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ አብርሐምን አመነው። አብርሐምም አንድ ቀን ቤተሰቦቹ ከሰማይ ከዋክብት ብዛት በላይ እንደሚያድጉ ጌታ የሰጠውን የተስፋ ቃል አመነ።

ዘፍጥረት 22፥17–18ያዕቆብ 4፥5