Scripture Stories
ንጉሥ ኢዮስያስ


“ንጉስ ኢዮስያስ፣” የብሉይ ኪዳን ታሪኮች [2022 (እ.አ.አ)]

“ንጉስ ኢዮስያስ፣” የብሉይ ኪዳን ታሪኮች

2 ነገሥት 222 ዜና 34–35

ንጉሥ ኢዮስያስ

የጌታን ትእዛዛት የመጠበቅ ተልዕኮ

ምስል
ወጣቱ ንጉሥ ኢዮስያስ

ኢዮስያስ የይሁዳ ንጉሥ ሆኖ በተሾመ ጊዜ የስምንት ዓመት ልጅ ነበር። ጌታን የሚወድ ጥሩ ንጉሥ ነበር። ጌታን እንዲታዘዙና ጣዖታትን ማምለክ እንዲያቆሙ ህዝቡን እስራኤላውያንን ለመርዳት ፈለገ። ዕድሜው ሲገፋ፣ እርሱና ህዝቡ ቤተመቅደሱን ማደስ እና እንደገና ውብ ማድረግ ጀመሩ።

2 ነገሥት 22፥1–22 ዜና 34፥3–7

ምስል
ኬልቅያስ በቤተመቅደሱ ፍርስራሽ ውስጥ የመፅሐፍ ጥቅልል​ ሲያገኝ

ህዝቡ በቤተመቅደሱ ላይ ሲሠሩ፣ የካህናቱ አለቃ ኬልቅያስ የህጉን መጽሐፍ፣ ቅዱሳት መጻሕፍትን የያዘውን ጥቅልል ​አገኘ።

2 ነገሥት 22፥3–9

ምስል
ያዘነው ንጉሥ ኢዮስያስ የህጉን መጽሐፍ ሲያዳምጥ

አንድ አገልጋይ መጽሐፉን ለኢዮስያስ አነበበለት። ኢዮስያስ ቃላቱን ሰማ እናም ሕዝቡ ጌታን ባለመታዘዙ ምክንያት አዘነ። ማዘኑን ለማሳየት ልብሱን ቀደደ።

2 ነገሥት 22፥10–13፣ 19

ምስል
የኢዮስያስ አገልጋዮች ከሕልዳ ጋር ሲነጋገሩ

ምን ማድረግ እንዳለባቸው ጌታን እንዲጠይቅ ለኪልቅያስ ነገረው። ኬልቅያስና የንጉሱ አገልጋዮች ሕልዳናን ጎበኙ። እርሷ ነቢይት ይሄውም በጌታ የተነሳሳች ታማኝ መሪ ነበረች። እርሷም ህዝቡ እንዲታዘዙ እየረዳ ስለነበር ጌታ በኢዮስያስ ተደስቷል አለች። ንጉስ ኢዮስያስ በሰላም እንደሚኖር ጌታ ቃል ገባ።

2 ነገሥት 22፥12–20

ምስል
ንጉሥ ኢዮስያስ በፋሲካ እራት ላይ

ንጉሥ ኢዮስያስ ህዝቡ ለጌታ የገቧቸውን ቃል ኪዳኖች እንዲጠብቁ ፈለገ። ጌታ ከረጅም ጊዜ በፊት እስራኤላውያንን እንዴት ከግብፅ ነፃ እንዳወጣቸው ለማስታወስ እንዲረዳቸው ፋሲካን እንዲያከብሩ ጠየቃቸው።

2 ዜና 35፥1–19