ምዕራፍ ፮
ያዕቆብ እንደገና የአይሁዶችን ታሪክ ተረከ፥ ስለባቢሎን ምርኮና መመለስ፤ ስለእስራኤሉ ቅዱስ አገልግሎትና ስቅለት፤ ከአህዛብ እርዳታን ስለማግኘታቸው፤ እና አይሁዶች በኋለኛው ቀን በመሲሁ ሲያምኑ ዳግሞ መመለሳቸውን። ፭፻፶፱–፭፻፵፭ ም.ዓ. ገደማ።
፩ የኔፊ ወንድም ያዕቆብ ለኔፊ ህዝብ የተናገራቸው ቃላት—
፪ እነሆ፣ የተወደዳችሁ ወንድሞቼ፣ በእግዚአብሔር የተጠራሁትና በቅዱስ ስርዓቱን መሰረት ሹመትን ያገኘሁት፣ እናም እርሱን እንደ ሀንጉስ ወይም ተከላካይ በምታምኑትና፣ በእርሱ ለጥበቃችሁ ተስፋ በምታደርጉ በወንድሜ ኔፊ የተቀባሁት እኔ ያዕቆብ፣ እነሆ፣ እኔ እጅግ ብዙ ነገሮችን እንደተናገርኳችሁ ታውቃላችሁ።
፫ ሆኖም እኔ እንደገና እናገራችኋለሁ፤ ምክንያቱም ለነፍሳችሁ ደህንነት ፍላጎት አለኝና። አዎን፣ ለእናንተ ጭንቀቴ ታላቅ ነው፤ እናም እናንተ ሁልጊዜ ይህ እንደሚሆን ታውቃላችሁ። እኔ በሙሉ ትጋት መክሬአችኋለሁ፤ እናም የአባቴን ቃል አስተምሬአችኋሁ፤ እናም ከዓለም መፈጠር ጀምሮ ሁሉንም የተፃፉ ነገሮች በተመለከተ አነጋግሬአችኋለሁ።
፬ እናም አሁን፣ እነሆ፣ ስላሉትና ስለሚመጡት ነገሮች እነግራችኋለሁ፤ ስለዚህ፣ ሀየኢሳይያስን ቃል አነብላችኋለሁ። እናም እነርሱ ወንድሜ ለእናንተ እንድናገር የፈለጋቸው ቃላት ናቸው። እናም የምናገራችሁ ለእናንተ ጥቅም፣ እናንተ አምላካችሁን ታውቁትና ስሙንም ታወድሱ ዘንድ ነው።
፭ እናም አሁን እኔ የማነባቸው ቃላት ኢሳይያስ የእስራኤልን ቤት በተመለከተ የተናገራቸው ናቸው፤ ስለሆነም፣ ከእናንተም ጋር ተመሳሳይነት አላቸው፣ ምክንያቱም እናንተ ከእስራኤል ቤት ናችሁና። እናም ከእስራኤል ቤት ስለሆናችሁ በኢሳይያስ የተነገሩ ለእናንተ የሚተገበሩ ብዙ ነገሮች አሉ።
፮ እናም አሁን፣ ቃላቱ እነዚህ ናቸው፥ ጌታ እግዚአብሔር ሀእንዲህ ይላል—እነሆ እጄን ወደ አህዛብ አነሳለሁ፣ ለአርማዬንም ወደ ወገኖች አቆማለሁ፤ ወንዶች ልጆችሽንም በክንዳቸው ያመጡአቸዋል፥ ሴቶች ልጆችሽንም በጫንቃቸው ይሸከሟቸዋል።
፯ ነገሥታትም አሳዳጊ አባቶችሽ ይሆናሉ፣ እቴጌዎቻቸውም ሞግዚቶችሽ ይሆናሉ፤ ፊታቸውን ወደ ምድር ዝቅ አድርገው ይሰግዱልሻል፣ የእግራችሁንም ትቢያ ይልሳሉ፤ እናም እኔ ጌታ መሆኔን ታውቂያለሽ፤ እኔን ሀየጠበቁ አያፍሩምና።
፰ እናም አሁን እኔ ያዕቆብ እነዚህን ቃላት በተመለከተ በመጠኑ እናገራለሁ። እነሆም ጌታ እኛ ከመጣንበት ሀበኢየሩሳሌም የነበሩት እንደተገደሉና በምርኮ ለእንደተወሰዱ አሳይቶኛል።
፱ ሆኖም፣ ጌታ እነርሱ እንደገና ሀእንደሚመለሱ አሳይቶኛል። እናም ደግሞ ጌታ እግዚአብሔር፣ የእስራኤሉ ቅዱስ፣ በስጋ እራሱን እንደሚገልፅላቸው፤ እናም መልአኩ ለእኔ በተናገረው ቃል መሠረት፣ እራሱን ከገለፀ በኋላ ይገርፉታልም ለይሰቅሉታልም።
፲ እናም በእስራኤሉ ቅዱስ ላይ ልባቸውን ካጠጠሩና አንገታቸውን ካደነደኑ በኋላ፣ እነሆ፣ የእስራኤል ቅዱስ ሀፍርድ በእነርሱ ላይ ይመጣል። እናም እነርሱ የሚቀጡበትና የሚሰቃዩበት ቀን ይመጣል።
፲፩ ስለሆነም፣ መላኩ እንዳለው፣ ወዲህና ወዲያ እንዲዘዋወሩ ከተደረጉ በኋላ፣ ብዙዎቹ በስጋ ይሰቃያሉ፣ በታማኝ ፀሎቶች የተነሳም እንዲጠፉ አይደረጉም፤ እነርሱ ይበተናሉ፣ ይገረፋሉ፣ እናም ይጠላሉ፤ ይሁን እንጂ፣ ጌታ ለእነርሱ መሀሪ ይሆናል፣ መድኃኒታቸውንም ሀሲያውቁት ወደ ርስት ምድራቸው በድጋሚ በአንድ ላይ ለይሰበሰባሉ።
፲፪ እናም ነቢያት የፃፉላቸው ሀአህዛብ የተባረኩ ናቸው፤ እነሆም፣ እነርሱ ንስሀ ከገቡና ከፅዮን ካልተዋጉ፣ እና እራሳቸውን ከታላቋና ለየርኩሰት ቤተክርስቲያን አንድ ካላደረጉ ይድናሉ፤ ጌታ እግዚአብሔር ለልጆቹ የገባውን ሐቃል ኪዳን ይፈፅማልና፤ እናም ለዚህ ነው ነቢዩ እነዚህን ነገሮች የፃፈው።
፲፫ ስለዚህ፣ ከፅዮን ጋርና ከጌታ የቃል ኪዳን ህዝብ ጋር የሚዋጉ የእግሮቻቸውን ትቢያ ይልሳሉ፤ እናም የጌታ ህዝቦች ሀአያፍሩም። የጌታ ህዝቦች እርሱን ለየሚጠብቁ ናቸውና፤ አሁንም የመሲሁን መምጣት ይጠብቃሉና።
፲፬ እናም እነሆ፣ በነቢዩ ቃላት መሠረት መሲሁ ሀለሁለተኛ ጊዜ እነርሱን ለማደስ እንደገና ይጀምራል፤ ስለዚህ፣ በእርሱ የሚያምኑበት ያ ቀን ሲመጣ፣ እራሱን በኃይልና በታላቅ ክብር ጠላታቸውን ለበመደምሰስ ሐይገልፃል፤ እናም በእርሱ የሚያምኑትን አንዳቸውንም አያጠፉም።
፲፭ እናም በእርሱ የማያምኑ ሀበእሳትና፣ በአውሎ ነፋስ፣ በመሬት መንቀጥቀጥና፣ በደም መፍሰስ፣ ለበቸነፈር፣ በረሀብና፣ በድርቅ ሐይጠፋሉ። እናም ጌታ እግዚአብሔር የእስራኤል ቅዱስ መሆኑን ያውቃሉ።
፲፮ ሀአደን ከሃያሉ ይወሰዳልን፣ ወይስ ለየህጋዊ ምርኮኞች ያመልጣሉን?
፲፯ ነገር ግን ጌታ እንዲህ ይላል፥ በኃያላን ሀየተማረኩትም እንኳን ይወሰዳሉ፣ የጨካኞችም አደን ያመልጣል፤ ለኃያሉ አምላክ የቃል ኪዳን ህዝቡን ሐያድናልና። ጌታም እንዲህ ይላል፥ ከእናንተ ጋር የሚጣሉትን እጣላቸዋለሁ—
፲፰ እናም አስጨናቂዎችሽን ስጋቸውን አስበላቸዋለሁ፤ እናም እንደጣፋጭ ወይን ጠጅ ደማቸውን ጠጥተው ይሰክራሉ፤ እናም ስጋ ለባሹም ሁሉ እኔ ጌታ መድኃኒትሽና ሀቤዛሽ የያዕቆብ ለኃያል እንደሆንኩ ያውቃሉ።