ምዕራፍ ፳፩
የእሴይ ግንድ (ክርስቶስ) በጻድቅነት ይፈርዳል—ስለእግዚአብሔር የሚኖረው እውቀት በአንድ ሺህ ዘመን ምድርን ይሞላል—ጌታም አርማውን ያነሳል እናም እስራኤልን ይሰበስባል—ኢሳይያስ ፲፩ን አነጻፅሩ። ከ፭፻፶፱–፭፻፵፭ ም.ዓ. ገደማ።
፩ እናም ሀከእሴይ ለግንድ ሐበትር ይወጣል፣ ከስሩም ቅርንጫፍ ይበቅላል።
፪ እናም የጌታ ሀመንፈስ፣ የጥበብና የመረዳት መንፈስ፣ የምክርና የኃይል መንፈስ፣ የእውቀትና እግዚአብሔርን የመፍራት መንፈስ በላዩ ላይ ያርፋል፤
፫ እናም በእግዚአብሔር ፍርሃት በፍጥነት የሚረዳ ያደርገዋል፤ እናም እርሱ በዐይኖቹ ባየው ሀአይፈርድም፣ ወይም በጆሮዎቹ በሰማውም አይገስጽም።
፬ ነገር ግን ድሆችን ሀበፅድቅ ይፈርዳል፣ ለምድር ለትሁቶችም በእኩልነት ሐይገስጻል፤ እናም ምድርን በአፉ በትር ይመታል፣ እናም ክፉዎችን በከንፈሮቹ እስትንፋስ ይገድላል።
፭ እናም ፅድቅ የወገቡ መታጠቅያ፣ ታማኝነትም የጎኑ ሀመታጠቅያ ይሆናሉ።
፮ ተኩላውም ደግሞ ከበጉ ጋር ይኖራል፣ አቦሸማኔው ደግሞ ከፍየል ጠቦት ጋር ይተኛል፣ ጥጃውም የአንበሳ ደቦልም፣ ፍሪዳውም በአንድነት ይሆናሉ፤ ታናሽ ልጅም ይመራቸዋል።
፯ እናም ላምና ድብ አብረው ይመገባሉ፤ ግልገሎቻቸውም በአንድነት ይተኛሉ፤ አንበሳውም እንደበሬ ገለባን ይበላል።
፰ እናም የሚጠባው ህፃን በመርዛማው እባብ ሀጉድጓድ ላይ ይጫወታል፣ ጡት የጣለውም ህፃን ለበእፉኝት ቤት ላይ ይጭናል።
፱ በተቀደሰው ተራራዬ ላይ ሁሉ ሀአይጎዱም፣ ወይም አያጠፉም፣ ውኃዎች ባህርን እንደሚሸፍን ሁሉ ምድር በጌታ ለእውቀትም ትሞላለችና።
፲ እናም ሀበዚያ ቀን ለህዝቡ ምልክት ሆኖ የሚቆም ለየእሴይ ስር ይኖራል፤ ሐአህዛብም መእርሱን ይፈልጋሉ፤ እናም የሚያርፍበትም የተከበረ ይሆናል።
፲፩ እናም በዚያ ቀን እንዲህ ይሆናል ጌታ የቀረውን የህዝቡን ቅሪት ከአሶርና፣ ከግብፅ፣ ከጳትሮስና፣ ከኩሽ፣ ከኢላምና፣ ከሰናዖር፣ ከሐማት፣ ከባህር ደሴቶች መልስ ዳግም ይሰበስብ ዘንድ ሀለሁለተኛ ጊዜ እጁን ይዘረጋል።
፲፪ እናም እርሱ ለሀገሮች ሀምልክትን ያቆማል፣ ከእስራኤልም ለየተሰደዱትን ይሰበስባል፣ እናም በአራቱም የምድር ማዕዘናት የተበተነውን ይሁዳን በአንድነት ሐይሰበስባል።
፲፫ ሀየኤፍሬም ምቀኝነት ደግሞም ይቆማል፣ የይሁዳም ጠላቶች ይጠፋሉ፤ ኤፍሬም ለበይሁዳ ሐአይቀናምና፣ እናም ይሁዳ ኤፍሬምን አያበሳጭም።
፲፬ ነገር ግን በምዕራብ በኩል በፍልስጤማውያን ትከሻ ላይ ሀእየበረሩ ይወርዳሉ፤ የምስራቆቹንም ጭምር በአንድነት ያጠፋሉ፤ እጃቸውንም በኤዶምና በሞአብ ላይ ያሳርፋሉ፤ እናም የአሞንም ልጆች ይታዘዙአቸዋል።
፲፭ እናም ጌታ የግብፃውያንን የባህር ሠርጥ ፈፅሞ ሀያጠፋል፤ በኃያል አውሎ ነፋሱም እጆቹን በወንዞች ላይ ያንቀጠቅጣል፣ ሰባትም ወራጆች አድርጎ ይከፋፍለዋል፣ ሰዎችንም በደረቁ ያሻግራል።
፲፮ እናም እርሱ ከግብፅ ምድር በወጣ ጊዜ ለህዝቡ ቅሪት ሆኖ ለሚቀሩት ከአሶር እስከ እስራኤል የሚደርስን ያህል ሀጎዳና ያኖርላቸዋል።