ቅዱሳት መጻህፍት
፪ ኔፊ ፳፪


ምዕራፍ ፳፪

በአንድ ሺህ ዘመን ሰዎች ሁሉ ጌታን ያወድሳሉ—እርሱም በመካከላቸው ይኖራል—ኢሳይያስ ፲፪ን አነጻፅሩ። ከ፭፻፶፱–፭፻፵፭ ም.ዓ. ገደማ።

እናም በዚያ ቀን እንዲህ ትላለህ—አቤቱ ጌታ፣ አመሰግንሀለሁ፤ በእኔ ብትቆጣም እንኳ ቁጣህን አብርደህልኛል፣ አፅናንተህኛልም።

እነሆ፣ እግዚአብሔር መድኃኒቴ ነው፤ አምናለሁ፣ እና አልፈራም፤ ጌታ ያህዌህ ጥንካሬዬና ዝማሬዬ ነውና፤ ደግሞም እርሱ መድኃኒቴ ሆኖአልና።

ስለዚህ፣ ውኃንም ከመዳን ጉድጓዶች በደስታ ትቀዳለህ።

እናም በዚያ ቀን እንዲህ ትላለህ—ጌታን አወድሱ፣ ስሙንም ጥሩ፣ በአህዛብም መካከል ስራውን አውጁ፣ ስሙም ከፍ ያለ እንደሆነ አስታውቁ።

ለጌታ ዘምሩ፤ እርሱ ታላቅ ስራን ሰርቶአልና፤ ይህም በምድር ሁሉ ታውቋል።

በፅዮን የምትኖሩ ሁሉ ጩሁ፣ እልልም በሉ፤ በመካከላችሁ ያለው የእስራኤሉ ቅዱስ ታላቅ ነውና።