Scripture Stories
ሳርያ


“ሳርያ፣” የመፅሐፈ ሞርሞን ታሪኮች

“ሳርያ፣” የመፅሐፈ ሞርሞን ታሪኮች [2023 (እ.አ.አ)]

1 ኔፊ 2–35

ሳርያ

የሴት የእምነት ጉዞ

ምስል
ሳርያ እና ሌሂ

ሳርያ ከቤተሰቧ ጋር በኢየሩሳሌም ኖረች። ባለቤቷ ሌሂ የእግዚአብሔር ነቢይ ነበር። አንድ ቀን፣ ሌሂ ከቤተሰቡ ጋር ኢየሩሳሌምን ለቆ እንዲሄድ ጌታ ነገረው።

1 ኔፊ 2፥1–3

ምስል
ሳርያ ስትጸልይ

ሳርያ በእግዚአብሔር እምነት ነበራት። እሷና ቤተሰቧ ቤታቸውን ለቀው ወጡ። ከሌሂ ጋር ወደ ምድረ በዳ ለመሄድ ሲሉ ወርቃቸውን እና ብራቸውን ተው።

1 ኔፊ 2፥4–5

ምስል
ሳርያ በምድረበዳ ውስጥ

ሳርያ እና ሌሂ ምግብ እና ሌሎች የሚያስፈልጋቸውን ነገሮች ወሰዱ። ለብዙ ቀናት ከተጓዙ በኋላ በምድረበዳ ለመኖር ድንኳን ተከሉ። ከዚያም መሠዊያ ሠሩ እንዲሁም ለሠጣቸው እርዳታ ጌታን አመሰገኑ።

1 ኔፊ 2፥4፣ 6–7፣ 15

ምስል
ሳርያ ተጨንቃ፣ ሌሂ በሩቅ እያለ

አንድ ቀን ጌታ የሳርያን እና የሌሂን ወንድ ልጆች ወደ ኢየሩሳሌም ሄደው የነሐስ ሰሌዳዎችን እንዲያመጡ ጠየቃቸው። ሳርያ ልጆቿ ባልተመለሱ ጊዜ ፈራች። የሞቱ መስሏት ነበር። ሌሂ ሳርያን አፅናናት። ጌታ ወንድ ልጆቻቸውን እንደሚጠብቃቸው ማመንን መረጡ።

1 ኔፊ 3፥1–2፣ 4–65፥1–6

ምስል
ሳርያ እና ሌሂ ልጆቻቸውን ሲቀበሉ።

ሳርያ ልጆቿ ከኢየሩሳሌም በተመለሱ ጊዜ በደስታ ተሞላች። አሁን ጌታ እንደጠበቃቸው አወቀች። ጌታ የጠየቀውን እንዲያደርጉ ኃይል እንደሚሰጣቸው አመነች። የሳርያ ቤተሰብ በሙሉ ተደስተው ነበር፣ እናም ጌታን አመሰገኑ።

1 ኔፊ 5፥7–9