Scripture Stories
አቢሽ


“አቢሽ፣” የመፅሐፈ ሞርሞን ታሪኮች [2023 (እ.አ.አ)]

አልማ 17–19

አቢሽ

ህዝቦቿ በኢየሱስ እንዲያምኑ እየረዳች

ምስል
አቢሽ በመንደር ውስጥ እየተራመደች

አቢሽ ላማናዊት ለነበረች ንግስት ትሰራ ነበር። አቢሽ ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ ከአባቷ ራእይ ተማረች። ለብዙ አመታት በኢየሱስ ታምን እና እርሱን ለመከተል ትፈልግ ነበር። ነገር ግን ለሌሎች ላማናውያን ገና አልነገረቻቸውም ነበር።

አልማ 19፥16–17

ምስል
አቢሽ ንግሥቲቱን፣ ንጉሡን እና አሞንን እየተመለከተች

አንድ ቀን፣ ላማናውያንን ስለ ኢየሱስ እና ስለ እግዚአብሔር ለማስተማር አሞን የሚባል ኔፋዊ ወደ መንግስቱ መጣ። ንግስቲቱ እና ንጉሱ አሞን ያስተማረውን አመኑ። ንግስቲቱ እና ንጉሱ ኢየሱስ ወደ ምድር እንደሚመጣ እና በእርሱ የሚያምኑ ሁሉ ስርየትን እንዲያገኙ እንደሚያደርግ አወቁ።

አልማ 17፥12–1318፥33–36፣ 39–4019፥9፣ 13

ምስል
አቢሽ ሁሉም ሰው መሬት ላይ ወድቆ እያየች

ንግስቲቱ እና ንጉሱ መንፈስ ቅዱስ ተሰምቷቸው በጣም ደስ ስላላቸው በመሬት ላይ ወደቁ። አሞን እና አገልጋዮቹም ወደቁ። ቆማ የነበረችው አቢሽ ብቻ ነበረች።

አልማ 19፥6፣ 13–16

ምስል
አቢሽ ብዙ ሰዎችን እያናገረች

አቢሽ ስለዚህ ተአምር ለሰዎች መናገር ፈለገች። ሰዎች የሆነውን ነገር ሲያዩ በእግዚአብሔር ኃይል እንደሚያምኑ ተስፋ አደረገች። ስለዚህ አቢሽ ከአንዱ ቤት ወደ ሌላው ሮጠች። እግዚአብሔር በንግሥቲቱና በንጉሡ ላይ ያደረገውን ሄደው እንዲያዩ ለህዝቡ ነገረቻቸው።

አልማ 19፥17

ምስል
ብዙ ሰዎች መሬት ላይ ያሉትን ሰዎችን እያዩ

ብዙ ሰዎች ወደ ንግሥቲቱ እና ንጉሱ ቤት መጡ። ንግስቲቱ፣ ንጉሱ እና አገልጋዮቻቸው ሁሉ የሞቱ ይመስሉ ስለነበር ተገረሙ።

አልማ 19፥18

ምስል
ሰዎች እየተከራከሩ

ሰዎቹ ግራ ገብቷቸው ነበር። በንግሥቲቱ እና በንጉሱ ላይ ስለሆነው ነገር ተከራከሩ።

አልማ 19፥19–21

ምስል
አቢሽ ተንበርክካ የንግሥቲቱን እጅ ይዛ

አቢሽ ስትመለስ ሰዎቹ ሲከራከሩ ተመለከተች። እነሱ የእግዚአብሔርን ኃይል ስላላዩ አዘነች። ከዚያም ንግስቲቱን በእጇ ይዛ አነሳቻት፣ ንግስቲቱም ቆማ ኢየሱስን አመሰገነች።

አልማ 19፥28–29

ምስል
ንጉሡና ንግሥቲቱ ከአቢሽና ከአሞን ጋር ቆመው

ንግስቲቱ የባሏን እጅ ያዘች እሱም ቆመ። ንጉሡም ለህዝቡ ስለ ኢየሱስ ተናገረ። ከዚያም አሞን እና ሌሎች አገልጋዮችም ተነሱ። ሁሉም ኢየሱስ እንደቀየራቸው ለሕዝቡ ነገሩ። አሁን መልካም ነገር ብቻ ለመስራት ፈለጉ። ብዙ ሰዎችም አመኑዋቸው።

አልማ 19፥29–36

ምስል
አቢሽ፣ ንግስቲቱ እና ንጉሱ ጥምቀትን እየተመለከቱ

አቢሽ ተስፋ እንዳደረገችው ሰዎች የእግዚአብሔርን ኃይል ተመለከቱ። ብዙ ሰዎች በኢየሱስ አመኑ እንዲሁም ተጠመቁ። የእግዚአብሔር መንፈስ ከእነሱ ጋር ነበረ። በምድራቸውም ቤተክርስቲያንን አቋቋሙ። ኢየሱስ ንስሐ የሚገባን እና በእርሱ የሚያምንን ሁሉ እንደሚረዳ ተመለከቱ።

አልማ 19፥17፣ 31፣ 35–36