ምዕራፍ ፫
አብርሐም ስለጸሀይ ጨረቃና ከዋክብት በኡሪምና ቱሚሙን መሰረት ተማረ—ስለመንፈሶች ዘለአለማዊነት ጌታ ገለጠለት—ከምድር በፊት ስለነበረው ህይወት፣ ስለቀድሞ መመረጥ፣ ስለፍጥረት፣ ስለአዳኝ ምርጫ፣ እና ስለሰው ዳግመኛ ሁኔታ ተማረ።
፩ እና እኔ አብርሐም በከለዳውያን ዑር ውስጥ ጌታ አምላኬ የሰጠኝ ሀኡሪምና ቱሚም ነበረኝ፣
፪ እና ሀከዋክብቱ ታላቅ እንደነበሩ፣ እና አንድያውም በእግዚአብሔር ዙፋን አጠገብ ቀርቦ ይገኝ እንደነበር አየሁ፤ እና በአጠገቡም የነበሩ ብዙ ታላላቆችም ነበሩ፤
፫ እና ጌታም እንዲህ አለኝ፥ እነዚህ ገዢዎች ናቸው፤ እና አጠገቤ ስለሆነና፣ የታላቁ ስም ሀቆሎብ ነው፣ እኔ ጌታ አምላክ ነኝና፥ ይህ ከቆምክበት አንድ አይነት ስርዓት ለሆኑት ሁሉ እንዲመራም ሰጥቼዋለሁ።
፬ በኡሪምና ቱሚም እግዚአብሔር እንዲህ አለኝ፥ ያ ቆሎብ በሚዞርበት ጊዜያትና ወቅቶች መሰረት፣ እንደ ጌታ ስርዓት አማካይነት ነው፤ እናም አምላክ እንደሚያውቀው የአንድ ሀቀን መዞሪያ፣ አንተ በቆምክበት ስፍራ እንደተሰጠው ሰአት አንድ ሺህ ለአመት ነው። ይህም በቆሎብ የሚቆጠረው ሰአት፣ አምላክ የሚቆጥርበት ሰአት ነው።
፭ ጌታም እንዲህ አለኝ፥ ታናሽ ብርሃን ያላት አለም፣ ቀኑን ከምታሰለጥነው በታች ብርሃን ያላት፣ እንዲሁም የማታው፣ አንተ አውቀሀት ከምትቆምባት አለም በላይ ታላቅ ነች፣ ይህች የምትሄደው በዝግታ ስለሆነ ነውና፤ ይህም ስርዓቱ የሆነበት ምክንያት ከቆምክበት መሬት በላይ ስለሚገኝ ነው፣ ስለዚህ የሚቆጠርበት ሰአቱ ከቀናት፣ ወራትና አመታት ቁጥር አይነት የሚበዛ አይደለም።
፮ ጌታም እንዲህ አለኝ፥ አሁን፣ አብርሐም፣ እነዚህ ሀሁለት እውነቶች አሉ፣ እነሆ አይኖችህ ይህን አይተዋል፤ አንተም የጊዜ አቆጣጠርን፣ እና ሰአትን እንድትወስን፣ አዎን፣ በቆምክበት ምድር ላይ ሰአትን ለመወሰን፣ እና ቀኑን እንድታሰለጥን ለተሰጣት ብርሀን ሰአትን ለመወሰን፣ እናም ማታውንም እንድትመራ ለተሰጣት ታናሽ ብርሀን ሰአትን ለመወሰን ስለተሰጣት እንድታውቅ ተሰጥቶሀል።
፯ አሁን ለታናሿ ብርሀን የተወሰነው ሰአት አንተ ከቆምክበት ምድር ከሚቆጠረው ጊዜ በላይ በጣም ረጅም ነው።
፰ እና እነዚህ ሁለት እውነቶች በሚገኙበት፣ ሌላ የሚበልጣቸው እውነትም ይገኛል፣ ይህም የጊዜ አቆጣጠሩ ከዚህ የሚበልጥ ሌላ አለምም አለ።
፱ እንደዚህም በጌታ ጊዜ አቆጣጠር ከሆነው ወደ ቆሎብ እስክትመጣ ድረስ፣ ከአንዱ አለም ውስጥ በአቆጣጠር ከሌላው የሚበልጥ አለ፤ ቆሎብም በእግዚአብሔር ዙፋን አጠገብ፣ አንተ በቆምክበት ስፍራ አይነት ሀስርዓት ካላቸው ሌሎች አለማትን እንድትመራ የተወሰነች ነች።
፲ እና ወደ እግዚአብሔር ዙፋን እስክትቀርብ ድረስ፣ ብርሀን እንዲሰጡ ለታዘዙት ከዋክብት ላይ እንዴት ጊዜ እንደሚቆጠሩ እንድታውቅ ተሰጥቶሀል።
፲፩ እንደዚህም እኔ አብርሐም ከጌታ ጋር ፊት ለፊት፣ አንድ ሰው ከሌላ ጋር እንደሚነጋገር ሀተነጋገርኩ፤ እና በእጁም ስለሰራቸው ስራዎችም ነገረኝ፤
፲፪ እና እንዲህም አለኝ፥ ልጄ ሆይ ልጄ ሆይ (እና እጁ ተዘርግቶ ነበር)፣ እነሆ እነዚህን ሁሉ ነገሮች አሳይሀለሁ። እና እጁን በአይኖቼ ላይ አደረገ፣ እና በእጁ የሰራቸውን እነዚያን ነገሮች አየሁ፣ እነርሱም ብዙ ነበሩ፤ እና በአይኔ ፊት ተባዙ፣ እና መጨረሻቸውንም ማየት አልቻልኩም።
፲፫ እና እንዲህም አለኝ፥ ይህ ሽኒሀህ፣ ይህም ጸሀይ ነው። እና እንዲህም አለኝ፥ ቆቆብ፣ ይህም ኮኮብ ነው። እና እንዲህም አለኝ፥ ኦሌያ፣ ይህም ጨረቃ ነው። እና እንዲህ አለኝ፥ ቆቃውቢም፣ ይህም ከዋክብት ማለት፣ ወይም በሰማይ ጠፈር ላይ የሚገኙት የነበሩ ሁሉም ታላቅ ብርሃናት ናቸው።
፲፬ እና እነዚህን ቃላት ጌታ ሲነግረኝ ምሽት ነበር፥ አንተን እና ከአንተ በኋላ የሚመጡትን ዘሮችህን ሀአበዛለሁ፤ እና አሸዋዎችን ለመቁጠር ከቻልክ፣ የአንተ ሐዘር ቁጥርም እንዲሁ ይሆናል።
፲፭ አምላክም እንዲህ አለኝ፥ አብርሐም፣ እነዚህን ቃላትን ትገልጽ፣ ወደግብፅ ከመግባትህ በፊት እነዚህን ነገሮች አሳየሁህ።
፲፮ ሁለት ነገሮች ቢኖሩ፣ እና አንዱም ከሌላው በላይ ቢሆን፣ ከእነርሱም በላይ የሚበልጡም ነገሮች ይኖራሉ፤ ስለዚህ ሀቆሎብ ካየሀቸው ቆቃውቢም በላይ ሁሉ ታላቅ ነው፣ ምክንያቱም ይህም ከሁሉም በላይ የቀረበ ስለሆነ ነው።
፲፯ አሁን፣ ሁለት ነገሮች ቢኖሩ፣ አንዱም ከሌላው በላይ ቢሆን፣ እና ጨረቃም ከምድር በላይ ብትሆን፣ ከዚያም ከዚህም በላይ የሆነ ሌላ አለም ወይም ኮኮብ ይኖራል፤ እና ጌታ አምላክህ ሀለሚያደርጋቸው ነገሮች ካልሆነ በስተቀር በልቡ ለማድረግ የሚያስብ ምንም ነገር የለም።
፲፰ ታላቅ ኮኮብ እንዴት ሰራ፤ ደግሞም፣ ሁለት መንፈሶች ከኖሩ፣ እናም አንዱ ከሌላው በላይ ባለእውቀት ከሆነ፣ ምንም እንኳን አንደኛው ከሌላው ባለእውቀት ቢሆንም እነዚህ መንፈሶች መጀመሪያ የላቸውም፤ ከዚህ በፊትም ኖረዋል፣ መጨረሻም አይኖራቸውም፣ ከዚህ በኋላም ይኖራሉ፣ እነርሱ ሀግኖሉም፣ ወይም ዘለአለማዊ ናቸውና።
፲፱ ጌታም እንዲህ አለኝ፥ እነዚህ ሁለት እውነቶች አሉ፣ ሁለት መንፈሶች አሉ፣ እናም አንዱ ከሌላው በላይ እውቀተኛ ነው፤ ከእነርሱ በላይ እውቀት ያለው ሌላም ይኖራል፤ እኔ ጌታ አምላክህ ነኝ፣ እኔም ሀከሁሉም በላይ እውቀተኛ ነኝ።
፳ ጌታ አምላክህ መላእክቱን ሰዶ ከኤልከናኽ ቄስ እጆች ሀአድኖሀል።
፳፩ ከእነርሱ ሁሉ መካከል እኖራለሁ፤ ስለዚህ አሁን ወደ አንተ ዘንድ፣ ከሁሉም ውስጥ ጥበቤ ታላቅ በሆነው፣ በእጄ ስለተሰሩት ሀስራዎች ልገልፅልህ ወርጄአለሁ፣ አይኖችህ ከመጀመሪያ ጊዜ ጀምሮ ካዩዋቸው ባለእውቀቶች ሁሉ ላይ ለበጥበብና በጥንቃቄ በበላይ ሰማይንና በበታች ምድርን እመራለሁና፤ ካየሀቸውም ባለእውቀቶች መካከል በመጀመሪያም ወርጄአለሁ።
፳፪ አሁን ለእኔ አብርሐም ጌታ አለም ከመመስረቱ ሀበፊት የነበሩትን ለባለእውቀቶችን አሳየኝ፤ ከእነዚህ መካከልም ብዙ ታላቅ እና ሐመኳንንትም ነበሩ።
፳፫ እና እግዚአብሔር እነዚህ ነፍሶች መልካም እንደሆኑ አየ፣ እና በመካከላቸውም ቆመ፣ እንዲህም አለ፥ እነዚህን መሪዎቼ አደርጋለሁ፤ መንፈስ ከሆኑት መካከል ቆሞ ነበርና፣ እና መልካምም እንደነበሩ አየ፤ እንዲህም አለኝ፥ አብርሐም፣ አንተ ከእነርሱ አንዱ ነህ፤ ከመወለድህ በፊትም ሀተመርጠህ ነበር።
፳፬ እና ከእነርሱም መካከል እግዚአብሔርን የሚመስል ሀአንድም ቆሞ ነበር፣ እና ከእርሱ ጋር ለነበሩትም እንዲህ አላቸው፥ እንወርዳለን፣ በዚያም ስፍራ አለና፣ እና እነዚህን ነገሮች እንወስዳለን፣ እና እነዚህ ሊኖሩበት የሚችሉበትን ለምድርን ሐእንሰራለን፤
፳፭ እና ጌታ አምላክ የሚያዛቸውን ማናቸውንም ነገሮች ሁሉ ሀእንደሚያደርጉ ለማየት፣ በዚህ ለእንፈትናቸዋለን፤
፳፮ እና ሀየመጀመሪያ ሁኔታቸውን የጠበቁትም ይጨመርላቸዋል፤ እና ይህን የመጀመሪያውን ሁኔታቸውን ያልጠበቁትም ከዚህ አይነት መንግስት ውስጥ የመጀመሪያው ሁኔታቸውን ከጠበቁት ጋር ክብር አይኖራቸውም፤ እና ለሁለተኛ ሁኔታቸውን የጠበቁትም በራሳቸው ላይ ሐክብር ከዘለአለም እስከ ዘለአለም ይጨመርላቸዋል።
፳፯ እና ሀጌታ እንዲህ አለ፥ ማንን እልካለሁ? እና አንዱም እንደ ለሰው ልጅ መለሰ፥ እዚህ አለሁ፣ እኔን ላከኝ። እና ሐሌላም መለሰ እና እንዲህም አለ፥ በዚህ አለሁ፣ እኔን ላከኝ። እና ጌታ እንዲህ አለ፥ የመጀመሪያውን እልካለሁ።
፳፰ እና ሀሁለተኛውም ተቆጣ፣ እና የመጀመሪያ ሁኔታውን አልጠበቀም፤ እናም በዚያም ቀን፣ ለብዙዎች ተከተሉት።