አጠቃላይ ጉባኤ
በተሰማን ህብረት ከእግዚአብሄር ጋር ኃይል እናገኛለን
የጥቅምት 2020 (እ.አ.አ) አጠቃላይ ጉባኤ


በተሰማን ህብረት ከእግዚአብሄር ጋር ኃይል እናገኛለን

የስሜት ህብረትን ስንፈልግ፣ ጥረታችንን የበለጠ ሙሉ ለማድረግ የእግዚአብሔርን ኃይል እንጠራለን።

የጎርደን እናት ሥራዎቹን ከጨረሰ ኬክ እንደምትሰራለት ነገረችው። የሚወደውን አይንት። ለእርሱ ብቻ። እነዚያ ሥራዎች እንዲጠናቀቁ ጎርደን ወደ ሥራ ሄደ ፤ እናቱ ድግሞ ኬኩን ሰራች። ታላቅ እህቱ ካቲ ከጓደኛዋ ጋር ወደ ቤት መጣች፡፡ ኬኩን አይታ እሷ እና ጓደኛዋ አንድ ቁራጭ ይሰጣችው ይችል እንደሆነ ጠየቀች።

“አይ” አለ ጎርደን፣ “የእኔ ነው። እናቴ ለኔ ነው የጋገረችው እና ማግኝት ነበረብኝ”።

ካቲ ታናሽ ወንድሟ ላይ ጮህችበት። እሱ በጣም ራስ ወዳድ እና ቆንቋና ነበር። እንዴት ይህን ሁሉ ለራሱ ብቻ ይወስዳል?

ከሰዓታት በኋላ ካቲ ጓደኛዋን ወደ ቤት ለመውሰድ የመኪናውን በር ስትከፍት፣ እዚያም ወንበሩ ላይ በጥሩ ሁኔታ የተጣጠፉ ሁለት ሶፍቶች ነበሩ፣ ሁለት ሹካዎች ከላይ ፣ እና ሁለት ቁራጭ ኬክ በሳህን ላይ ተቀምጧል። ካቲ ይህንን ታሪክ በጎርደን የቀብር ሥነ ሥርዓት ላይ ስትናገር እሱ ምን ያህል ለመለወጥ ፈቃደኛ መሆኑን ለማሳየት እና ሁልጊዜ ደግነት ለማይገባቸው ሰዎች ደግነትለማሳየት ነው።

በ1842 (እ.አ.አ) ቅዱሳን የናቩ ቤተመቅደስን ለመገንባት ጠንክረው እየሠሩ ነበር። የሴቶች መረዳጃ ማህበር በመጋቢት ውስጥ ከተመሰረተ በኋላ፣ ነቢዩ ጆሴፍ ብዙ ጊዜ ወደ ስብሰባዎቻቸው እየመጣ በቤተመቅደስ ውስጥ በቅርቡ ለሚፈጽሟቸው ቅዱስ እና የአንድነት ቃል ኪዳኖች እነሱን ያዘጋጃቸው ነበር።

በሰኔ 9 ነቢዩ “ሰለ ምህረት እሰብካለሁ አለ። ኢየሱስ ክርስቶስ እና [መላእክቱ] በእኛ ላይ ጥቃቅን በሆኑ ነገሮች ይቆጣሉ ብለን እናስብ፣ ምን እንሆን ይሆን? መሐሪ መሆን እና ጥቃቅን ነገሮችን ችላ ማለት አለብን።” ፕሬዘደንት ስሚዝ ቀጠሉ ፣ “የተሟላ ህብረት አለመኖሩ ያሳዝነኛል - የአንድ አባል ስቃይ ሁሉም ይሰማው - በተሰማን ህብረት ከእግዚአብሄር ጋር ኃይል እናገኛለን።”1

ያ ትንሽ ዓረፍተ ነገር እንደ መብረቅ ወደቀብኝ። በተሰማን ህብረት ከእግዚአብሄር ጋር ኃይል እናገኛለን። ይህ ዓለም እኔ እንደምፈልገው አይደለም። ተጽዕኖ ማሳደር እና የተሻለ ማድረግ የምፈልጋቸው ብዙ ነገሮች አሉ። እና በግልፅ ፣ እኔተስፋ በማደርገው ላይ ብዙ ተቃውሞዎች አሉ ፣ እና አንዳንድ ጊዜ አቅም እንደሌለኝ ይሰማኛል። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ራሴን የሚፈትሹ ጥያቄዎችን እየጠየቅኩት ነው፤ በዙሪያዬ ያሉትን ሰዎች በተሻለ ለመረዳት የምችለው እንዴት ነው? ሁሉም በጣም የተለያዩ ሲሆኑ ያንን “የስሜት ህብረት” እንዴት መፍጠር እችላለሁ? ? ከሌሎች ጋር ይበልጥ ከተዋወቅኩ ከእግዚአብሄር ምን ኃይል ማግኘት እችላለሁ? ከነፍሴ ፍለጋ ሶስት አስተያየቶች አሉኝ። ምናልባት እናንትንም ሊጠቅሟችሁ ይችላሉ።

ምህረት አድርጉ

ያዕቆብ 2:17 “ወንድሞቻችሁ እንደ እራሳችሁ አስቡአቸው፣ እናም እነርሱም ልክ እንደ እናንተ ሀብታም ይሆኑ ዘንድ፣ ከሁሉም ጋር ተገናኚ እናም በንብረታችሁ ነፃ ሁኑ” ይላል። እስቲ ንብረት የሚለውን ቃል በምህረት—እንተካ፤ እንደ እናንተ ሀብታም እንዲሆኑ በምህረታችሁ ነፃ ሁኑ።

ብዙውን ጊዜ ስለ ንብረት በምግብ ወይም በገንዘብ ረገድ ነው የምናስበው ነገር ግን ምናልባት ሁላችንም በአገልግሎታችን የበለጠ የምንፈልገው ምህረትን ነው።

የራሴ መረዳጃ ማህበር ፕሬዝዳንት በቅርቡ “እኔ … ቃል የገባሁላችሁ ነገር ቢኖር … ስማችሁን በደህና እጠብቃለሁ የሚል ነው። … በምርጥ ሁኔታችሁ ማን እንደሆናችሁ አያለሁ። … በጭራሽ ስለእናንተ ደግነትን የጎደለው ፣ ከፍ ሊያደርጋችሁ የማይችል ምንም ነገር አልናገርም። ለእኔ እንዲሁ እንድታደርጉ እጠይቃለሁ ምክንያቱም በግልፅ እኔ እናንተን ማስከፋት ያስፈራኛል።”

ጆሴፍ ስሚዝ በዚያ ሰኔ በ1842 (እ.አ.አ) ለእህቶች ነገራቸው፤

“ሰዎች አነስተኛውን ደግነት እና ፍቅር ለእኔ ሲገልጹልኝ ፣ በአእምሮዬ ላይ እጅግ ኃይል አለው። …

ወደ ሰማያዊ አባታችን በይበልጥ ስንቀርብ የሚጠፉ ነፍሳትን የበለጠ በርህራሄ ለመመልከት እንወዳለንእነሱን በትከሻችን ላይ ለመሸክም እና ኃጢአታቸውን ከጀርባችን ላይ መጣል [ እንደምንፈልግ ይሰማናል]። [ንግግሬ የታሰበው] ለዚህ ሁሉ ህብረተሰብ ነው — እግዚአብሔር ምህረት እንዲያደርግላችሁ ብትወዱ ፣ እርስ በርሳችሁ ይቅር ተባባሉ።2

ይህ በተለይ ለመረዳጃ ማህበር ምክር ነበር። እርስ በርሳችን አንፈርድ ወይም ቃላቶቻችን እንዲነክሱ አንፍቀድ። አንዳችን የሌላችንን ስም ደህንነት እንጠብቅ እናም የምህረትን ስጦታ እንስጥ።3

ጀልባችሁ ይወዛወዝ

እ.ኤ.አ. በ 1936 ከዋሽንግተን ዩኒቨርሲቲ አንድ ግልጽ ያልሆነ የቀዛፊ ቡድን ወደ ጀርመን በኦሎምፒክ ጨዋታዎች ለመሳተፍ ተጓዘ። የታላቁ የኢኮኖሚ ውድቀት ጠለቅ ብሎ ነበር። እነዚህ ሰራተኛ ወንዶች አነስተኛ የማዕድን ማውጫ እና የእንጨት ከተሞች ወደ በርሊን እንዲጓዙ ገንዘብ የለገሷቸው ናቸው። ሁሉም የውድድሩ ገፅታዎች በእነሱ ላይ ተከምሮ ነበር ነገር ግን በውድድሩ ውስጥ አንድ ነገር ተከሰተ። በመርከቡ ዓለም ውስጥ “ዥዋዥዌ” ብለው ይጠሩታል። በጀልባ ውስጥ ያሉ ወንዶችበተሰኘው መጽሐፉ ላይ ተመስርተው ይህንን መግለጫ ያዳምጡ፤

አንዳንድ ጊዜ ለማሳካት እና ለመግለፅ ከባድ የሆነ የሚከሰት አንድ ነገር አለ። “መወዛወዝ” ይባላል። ይህ የሚሆነው ሁሉም ተመሳሳይ በሆነ አንድነት ሲቀዝፉ ብቻ ነው ፣ አንድም እርምጃ ከመመሳሰል ውጭ አይሆንም።

ቀዛፊዎች በሃይለኛ ነፃነታቸው ውስጥ መንገስ እና በተመሳሳይ ጊዜ ለግለሰባዊ ችሎታዎች ታማኝ መሆን አለባቸው። ውድድሮች በዘረመል አይሸነፉም። ጥሩ ቡድን ጥሩ ውህዶች ናቸው ፤ አንድ ሰው ኃላፊነትን የሚመራ ፣ አንድ ሰው በመጠባበቂያ አንድ ነገር ለመያዝ ፣ አንድ ሰው ውጊያን ለመዋጋት ፣ አንድ ሰው ሰላምን ለመፍጠር። አንድ ቀዛፊ ከሌላው የበለጠ ዋጋ የለውም ፣ ሁሉም ለጀልባው ባለድርሻ ናቸው፣ ነገር ግን በደንብ አብረው መቅዘፍ ካለባቸው፣ እያንዳንዳቸው ለሌሎችን ፍላጎቶች እና ችሎታዎች ማስተካከል አለባቸው፤ አጭር እጅ ያለው ሰው ትንሽ ወደ ፊት ሲደርስ ረዥም እጅ ያለው ሰው በጥቂቱ ወደ ውስጥ ይገባል።

ልዩነቶች ከጥፋት ይልቅ ወደ ጥቅም ሊለወጡ ይችላሉ። ከዚያ በኋላ ብቻ ነው ጀልባው በራሱ የሚንቀሳቀስ ሆኖ ሚታየው። ያኔ ብቻ ነው ህመም ሙሉ በሙሉ ለደስታ መንገድ የሚሰጠው። ጥሩ “ዥዋዥዌ” እንደ ግጥም ነው።4

ከፍ ካሉ መሰናክሎች ጋር ይህ ቡድን ፍጹም መወዛወዝን አገኘ እና አሸነፈ። የኦሎምፒክ ወርቅ አስደሳች ነበር ፣ ነገር ግን እያንዳንዱ ቀዛፊ ያንን ቀን ያጋጠማቸው አንድነት በሕይወታቸው ሙሉ ከእነሱ ጋር የቆየ፣ የተቀደሰ ጊዜ ነበር።

ጥሩው በፍጥነት እንዲያድግ መጥፎውን አርቁ

በጥሩ ምሳሌያዊ አነጋገር ያዕቆብ 5ውስጥ ፤ የወይኑ አትክልት ስፍራ ጌታ በጥሩ መሬት ላይ ጥሩ ዛፍ ተተከለ ፤ ነገር ግን ከጊዜ በኋላ ተበላሽቶ የዱር ፍሬን አፈራ። የወይኑ አትክልት ስፍራ ጌታ ስምንት ጊዜ “ይህን ዛፍ ማጣቴ በጣም ያሳዝነኛል” ብሏል።

ነገር ግን “እነሆ፣ አገልጋዩ ለወይኑ ስፍራ ጌታ አለው—ለትንሽ ጊዜ አቆየው። እናም ጌታውም አለ፣ አዎን ለትንሽ ጊዜ እተወዋለሁ ” ።5

እናም በራሳችን አነስተኛ የወይን እርሻዎች ውስጥ ቆፍረን ጥሩ ፍሬ ለማግኘት ለምንሞክር ለሁላችን ሊተገበር የሚችል መመሪያ ይመጣል ፡፡ “መልካሙ በሚያድግበት መሰረት መጥፎውን ታስወግዳላችሁ።”6

አንድነት በአስማት አይከሰትም; ሥራ ይጠይቃል። የተዝረከረከ ነው ፣ አንዳንድ ጊዜ የማይመች እና ጥሩው እያደገ በሄደ መጠን መጥፎውን ስናስወግድ ቀስ በቀስ የሚከሰት ነው።

አንድነት ለመፍጠር በምናደርገው ጥረት መቼም ብቸኛ አይደለንም። በመቀጠልምያዕቆብ 5 “አገልጋዮቹሄዱና መአቅማቸው ሰሩ ፡፡ የወይን ስፍራ ጌታ ደግሞም ከእነርሱ ጋር ሰራ።”7

እያንዳንዳችን ከባድ የመቁሰል አጋጣሚዎች ፣ በጭራሽ መሆን የሌለባቸው ነገሮች ሊኖሩን ነው። እያንዳንዳችን በተለያዩ ጊዜያት ትዕቢት እና ኩራት ያፈራነውን ፍሬ እንዲበላሽ እንፈቅዳለን። ነገር ግን ኢየሱስ ክርስቶስ በሁሉ ነገሮች አዳኛችን እና ቤዛችን ነው። የእርሱ ኃይል እስከ ታችኛው ክፍል ድረስ ይደርሳል እናም ስንጠራው በአስተማማኝ ሁኔታ ለእኛ አለ። ሁላችንም ስለ ኃጢአታችን እና ውድቀታችን ምህረትን እንለምናለን። በነፃ ይሰጠናል። እናም እሱ ያንኑ ተመሳሳይ ምህረት እና መረዳዳት ለሌላው መስጠት እንድንችል ይጠይቀናል።

ኢየሱስ በግልጽ አስቀምጧል “እንዲህ እላችኋለሁ፣ አንድ ሁኑ፤ እናም አንድ ካልሆናችሁ የእኔ አይደላችሁም።”8 ነገር ግን እኛ አንድ ከሆንን - ከኬካችን አንድ ቁራጭ ማስቀረት ወይም ጀልባው በፍፁም አንድነት መወዛወዝ እንዲችል የግል ችሎታዎችን የምንመጥን ከሆነ - እኛ የእርሱ ነን። እናም መልካሙ ባደገ ቁጥር በቶሎ መጥፎዎቹን ለማፅዳት ይረዳል።

ትንቢታዊ ተስፋዎች

እኛ በምንፈልገው ቦታ ላይ ላንሆን እንችላለን፣ እናም አሁን የምንሆንበት ቦታ ላይ አይደለንም። በራሳችን እና እኛ አባል በሆንባቸው ቡድኖች ውስጥ የምንፈልገው ለውጥ በአናሳ ንቅናቄ እና በየቀኑ እርስ በእርስ ለመረዳዳት ይበልጥ በንቃት በመሞከር እንደሚመጣ አምናለሁ። ለምን? ምክንያቱም “አንድ ልብና አንድ አእምሮ” የሆነችውን ጽዮንን እየገነባን ስለሆነ ነው።9

እንደ ቃልኪዳን ሴቶች እኛ ሰፊ ተጽዕኖ አለን። ይህ ተጽዕኖ ከጓደኛችን ጋር በምንማርበት ጊዜ ፤፣ ልጆችን እንዲተኙ ስናደርግ ፣ በአውቶቡሱ ውስጥ አብሮን ከተቀመጠ ስው ጋር ስናወራ፣ ከሥራ ባልደረባ ጋር የዝግጅት አቀራረብን ስናዘጋጅ በሁሉ ጊዜችን ውስጥ ይሠራል። ጭፍን ጥላቻን ለማስወገድ እና አንድነትን ለመገንባት ኃይል አለን።

የሴቶች መረዳጃ ማህበር እና ወጣት ሴቶች ቀላል ክፍሎች አይደሉም። የእኛን ዥዋዥዌእስክናገኝ ድረስ በጣም የተለያዩ ሴቶች ሁሉም ወደ አንድ ጀልባ የሚገቡበት እና ተራ የሚይዙባቸው የማይረሱ ልምዶች ሊሆኑ ይችላሉ ዓለምን ለመልካም ወደሚለውጥ የጋራ ኃይል አካል እንድትሆኑ ይህ ግብዣዬ ነው። የቃል ኪዳን ተልእኳችን ማገልገል ፣ የወድቁትን እጆች ማንሳት ፣ በትግል ላይ ያሉ ሰዎችን በጀርባችን ወይም በእጃችን ላይ አድርገን እነሱን መሸከም ነው። ምን ማድረግ እንዳለብን ማወቅ ውስብስብ አይደለም ፣ ነገር ግን ብዙውን ጊዜ ከራስ ወዳድ ፍላጎቶቻችን ጋር ይጋጫል እናም መሞከር አለብን። የዚህች ቤተክርስቲያን ሴቶች ህብረተሰቡን ለመለወጥ ያልተገደበ አቅም አላቸው። የስሜት ህብረትን ስንፈልግ ፣ ጥረታችንን ሙሉ ለማድረግ የእግዚአብሔርን ኃይል እንደምንጠራ ሙሉ መንፈሳዊ እምነት አለኝ።

ቤተክርስቲያኗ 1978 (እ.አ.አ) የክህነት ራእይ ስትዘክር ፣ፕሬዘዳንት ራስል ኤም ኔልሰን ኃይለኛ ትንቢታዊ በረከትን አስተላልፏል-“ማንኛውንም የጭፍን ጥላቻ ሸክምን አሸንፈን ከእግዚአብሄር ጋር እንዲሁም በአንድነት ፍጹም የሆነ ሰላም እና ስምምነት እንዲኖረን ለሚሰሙኝ ሁሉ የምተወው ጸሎቴ እና ቡራኬዬ ነው።”10

ይህንን ትንቢታዊ በረከት በዓለም ውስጥ በግለሰብ እና በጋራ ጥረታችን አንድነትን ለማሳደግ እንጠቀም። ምስክርነቴን በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ ትሁት ፣ ጊዜ የማይሽረው ጸሎት ቃላት እተውላችኃለሁ፤ “አባት ሆይ፥ በእኔ እንዳለህ እኔም በአንተ፥ እነርሱ ደግሞ በእኛ አንድ ይሆኑ ዘንድ እለምናለሁ።”11 በኢየሱስ ክርስቶስ ስም፣ አሜን።