አጠቃላይ ጉባኤ
በጌታ እጅግ የተወደደ
የጥቅምት 2020 (እ.አ.አ) አጠቃላይ ጉባኤ


በጌታ እጅግ የተወደደ

የመከራ እና የጭንቀት ጊዜያት እርሱ እኛን ሲመለከት፣ ሲባርክ የጌታን የሚጠብቀውን አይን አይለውጡትም።

ከብዙ አመታት በፊት አንድ ቀን፣ በአማሚ ኦሺማ፣ ጃፓን ትንሽ ደሴት ላይ በትንሽ ቅርንጫፍ ውስጥ እንደ ወንጌን ሰባኪ በማገለግልበት ጊዜ፣ ፕሬዝዳንት ስፔንሰር ደብሊው. ኪምቦል እስያ እየጎበኙ መሆናቸውን ስንረዳ እና በጃፓን ያሉ ሁሉም አባላት እና ሚስዮናውያን በአካባቢው ጉባኤ ላይ ነቢዩን በግል ለመስማት ወደ ቶኪዮ እንደተጋበዙ ስንገነዘብ በጣም ተደስተን ነበር። ከቅርንጫፍ አባላት ጋር፣ የሚስዮን ጓደኛዬ እና እኔ በጉባኤው ላይ ለመገኘት በመደሰት፣ የምስራቅ ቻይና ባህር አቋርጠው ወደ ዋናው ጃፓን ለመድረስ የ12 ሰዓት የጀልባ ጉዞ፣ እና ከዚያ በኋላ ወደ ቶኪዮ የ15 ሰዓት የባቡር ጉዞ እቅድ ማውጣት ጀመርን። የሚያሳዝን ሆኖም አልተሳካም። እኔ እና ጓደኛዬ በርቀት እና በጊዜ ምክንያት በቶኪዮ በተደረገው ጉባኤ ላይ ለመሳተፍ እንደማንችል ከተልእኮ ፕሬዚዳንታችን መልእክት ደረሰን።

ምስል
ሽማግሌ ስቲቨንሰን እና የሚስዮናዊ ጓደኛቸው

የትንሿ ቅርንጫፋችን አባላት ወደ ቶክዮ ሲያቀኑ፣ እኛ ከኋላ ቀረን። በቀጣዮቹ ቀናት ጸጥ ያለ እና ባዶ ይመስል ነበር። የኋለኛው ቀን ቅዱሳን እና የጃፓን ሚስዮናውያን በጉባው ሲሳተፉ፣ እኛ በትንሿ የቤተክርስቲያኗ መሰብሰቢያ ቤት ውስጥ ብቻችንን የቅዱስ ቁርባን ስብሰባ አካሄድን።

ምስል
የእስያ ክልል ጉባኤ

የቅርንጫፍ አባላትን ከቀናት በኋላ ፕሬዝዳንት ኪምቦል በቶኪዮ ቤተመቅደሱ እንደሚገነባ አስታውቀዋል በማለት ከጉባኤው ተመልሰው ሀተታ ሲሰጡ በደስታ ባዳምጥም እንኳን፣ የግል ኪሳራዬ ስሜት ተጠናክሮ ነበር። የሕልማቸውን ፍፃሜ ሲካፈሉ በጣም ተደሰቱ። የቤተመቅደሱን ማስታወቂያ በሰሙ ጊዜ አባላት እና ሚስዮናውያን ደስታቸውን መቆጣጠር እንዳልቻሉ እና በድንገት ማጨብጨብ እንደጀመሩ ገለጹ።

ምስል
ፕሬዝዳንት ኪምቦል በቶኪዮ ቤተመቅደስ እንደሚገነባ ሲያስተዋውቁ

ዓመታት አለፉ፣ እናም በታሪካዊው ስብሰባ መሳተፍ አለመቻሌን በማወቄ የተሰማኝን ብስጭት አሁንም አስታውሳለሁ።

በአለፉት ወራት የአለም አቀፍ COVID-19 ወረርሽኝ እኔ ከነበረኝ አጋጣሚ በላይ በወጣት ሚስዮናዊነት በጣም የሚያበሳጭ አጋጣሚዎችን ሲያገኙ በማየቴ ይህንን ተሞክሮ አስብበት ነበር።

በዚህ ይር መጀመሪያ ላይ፣ ወረርሸኙ በፍጥነት እየተስፋፋ ሲሄድ፣ ቀዳሚ አመራር “ቤተክርስቲያኗ እና ምዕመናን ጥሩ ዜጎች እና ጥሩ ጎረቤቶች ለመሆን ያለንን ቁርጠኝነት በታማኝነት ያሳያሉ”1 እናም“ሀይለኛ ጥንቃቄ ያደርጋሉ”2በማለት ቃል ገብተዋል። ስለሆነም፣ በዓለም ዙሪያ ያሉ የቤተክርስቲያን ስብሰባዎች መታገድ፣ ከግማሽ በላይ የቤተክርስቲያኗ ሚስዮናዊ ኃይል ወደ ትውልድ አገራቸው መመለሱን፣ እና በመላው ቤተክርስቲያኗ ውስጥ ሁሉም ቤተመቅደሶች መዘጋታቸውን ተመልክተናል። በሺዎች የምትሚቆጠሩትም ለግል መንፈሳዊ ሥነ-ሥርዓቶች፣ እንዲሁም ለመታተም፣ ወደ ቤተመቅደስ ለመግባት እየተዘጋጃችሁ ነበር። ሌሎቻችሁም ቀደም ብላችሁ የሚስዮናዊነት አገልግሎታችሁን አጠናቅቃችኋል ወይም ለጊዜው ተለቅቃችኋል እና በሌላ ተመድባችኋል።

ምስል
ወንጌል ሰባኪዎች በኮቪድ ምክንያት ሲመለሱ

በዚህ ወቅት የመንግስት እና የትምህርት አመራሮች ትምህርት ቤቶችን ዘግተው ነበር፣ በዚህም ምክንያት የምረቃ ለውጥን የቀየረ እና የስፖርት እና ሌሎች ከትምህርት ቤት ጋር የተዛመዱ ዝግጅቶች እና እንቅስቃሴዎች እንዲሰረዙ ያስገደደ ነበር። ብዙዎቻችሁ ላልተሰሙ ትርኢቶች እና ውድድሮች ወይም ያልተጫወቱ የአትሌቲክስ ወቅቶች ተዘጋጅታችሁ ነበር።

በዚህ ወቅት የሚወዷቸውን በጣም የሚያሳዝነው በሞት ውድ ቤተሰቦቻቸውን ስላጡት ሀሳቦች ናቸው፤ ብዙዎች እንዳሰቡት የቀብር ሥነ ሥርዓቶችን ወይም ሌሎች የማስታወሺያ ስብሰባዎችን ማድረግ አልቻሉም ነበር።

በአጭሩም፣ ብዙዎቻችሁ በጣም እውነተኛ ብስጭት፣ ሀዘን እና ተስፋ መቁረጥ ደርሶባችኋል። ታዲያ ለመፈወስ፣ ለመፅናት፣ እና በእምነት ወደፊት ለመግፋት እንዴት እንችላለን?

ነብዩ ኔፊ ጎልማሳ ከሆነ ነበር ትንሾቹ ሰሌዳዎችን መቅረጽ የጀመረው። ወደ ህይወቱ እና አገልግሎቱ ወደ ኋላ ሲመለከት፣ በመፅሐፈ ሞርሞን የመጀመሪያ ቁጥር ላይ አስፈላጊ ነጸብራቅ አቅርቧል። ይህ ጥቅስ በእኛ ጊዜ ልናስብ የሚያስፈልገንን መርህ ያስቀምጣል። “እኔ ኔፊ፣ ከመልካም ወላጆች የተወለድኩ በመሆኔ …፣” ከሚሉት የተለመዱትን ቃሎቹን በመከተል እንዲህ ጻፈ፣ “እናም በዘመኔም ብዙ መከራን ብመለከትም፣ በጊዜዬ ሁሉ ከጌታ ድጋፍን [አግኝቻለሁ]።”3

እንደመፅሐፈ ሞርሞን ተማሪዎች፣ ኔፊ የሚጠቅሳቸውን ብዙ መከራዎች እናውቃለን። ሆኖም በእሱ ቀናት ውስጥ ለደረሰበት መከራዎች እውቅና መስጠቱን ተከትሎ፣ ኔፊ በሁሉም ቀናት ውስጥ በጌታ ዘንድ በጣም የተወደደ የመሆንን የወንጌል እይታ ይሰጣል። የመከራ እና የጭንቀት ጊዜያት እርሱ እኛን ሲመለከት፣ ሲባርክ የጌታን የሚጠብቀውን አይን አይለውጡትም።

ምስል
ምናባዊ የሚስዮን ስብሰባ
ምስል
ምናባዊ ስብሰባ ከሽማግሌ እና እህት ስቲቨንሰን ጋር
ምስል
ምናባዊ ስብሰባ ከሽማግሌ እና እህት ስቲቨንሰን ጋር

ሌሳ እና እኔ በቅርቡ ከአውስትራሊያ 600 የሚሆኑ ሚሰኦናዊያንን ምናባዊ ስብሰባ አግኝቼ ነበር፣ አብዛኞቻቸው በኮቪድ-19 ምክንያት ተነጥለው ወይም ታግድው ነበር፣ አብዛኞቹ ከቤት ሆነው ይሰሩ ነበር። በአንድነት፣ በአዲስ ኪዳን፣ በመፅሐፈ ሞርሞን እና በትምህርት እና ቃል ኪዳኖች ውስጥ በመከራ ጊዜ ታላቅነትን እንዲያከናውኑ ጌታ የባረካቸውን ግለሰቦች አስታውሰናል። ሁሉም የታወቁበት በታሰሩበት እና በተገደቡበት ጊዜያቸው ለማድረግ ባልቻሉበት ሳይሆን በጌታ እርዳታ ማድረግ በቻሉት ነበር።

ጳውሎስና ሲላስ በአክሲዮን ታስረው እያሉ እንደጸለዩ፣ እንደዘምሩ፣ እንዳስተምሩ፣ እንደመሰክሩ፣ እንዲሁም የእስር ቤቱን ጠባቂ እንኳን እንደጠመቁ እናነባለን።4

እንደገናም ጳውሎስ በሮሜ ውስጥ በቤት ውስጥ ለሁለት አመት ተገድቦ እያለ፣ በዚህም ጊዜ “ስለእግዚአብሔር መንግስት መመስከር”5 እናም “ስለኢየሱስ ክርስቶስ እጅግ ገልጦ [በማስተማር]”6ቀጠለ።

ከተጎሳቀሉ እና በእስር ቤት ከተጣሉ በኋላ፣ የሔላማን ወንድ ልጆች ኔፊ እና ሌሂ በእሳት ተከብበው ሲጠበቁ የጌታ “ፍፁም የሆነ እርጋታ ያለው ለስላሳ ድምፅ … [የአጋቾቻቸውን] ነፍስንም እንኳን የሚወጋ ነበር።”7

በአሞኒሀ ውስጥ የነበሩት አልማ እና አሙሌቅ “ብዙዎች … አመኑ፣ እናም ንስሃ መግባትና ቅዱሳት መጻሕፍትን መመርመር ጀመሩ”8 ፣ይህም የሆነው ምንም እንኳን እነርሱ ተሳልቆባቸው እና ያለምግብ፣ ውሀ፣ ወይም ልብስ በእስር ቤት ታስረው እና ተገድበው በነበረበት ጊዜ ነበር።9

ምስል
ጆሴፍ ስሚዝ በልብርቲ እስር ቤት

እናም በመጨረሻ ጆሴፍ ስሚዝ፣ የተተወ እና ጌታ የተደበቀ እንደሆነ ስሜት እየተሰማው በልብረቲ እስር ቤት እየተሰቃየ ሳለ፣ “እነዚህ ነገሮች ሁሉ ለአንተ ልምድ”10 ነው እና “እግዚአብሔር ለዘለአለም ከአንተ ጋር ነውና”11የሚለውን የጌታ ቃል ሰማ።

እያንዳንዱም ኔፊ ያውቅ የነበረው ገብቷቸዋል፤ በጊዜያቸው እንኳን ብዙ መከራን አይተው ቢሆንም፣ በጌታ እጅግ የተወደዱ ነበሩ።

እንደ ግለሰብ አባላት እና እንደ ቤተክርስቲያን ላለፉት በርካታ ወራቶች ባጋጠሙን ፈታኝ ጊዜያት እኛም በጌታ ከፍተኛ ሞገስ እንዳገኘን ትይዩዎችን መሳል እንችላለን። እነዚህን ምሳሌዎች ስጠቀስ፣ እነርሱም የመጡትን ተግዳሮቶች እንድንቋቋም የሚያስችለንን ማስተካከያዎችን ከማንኛውም ወረርሽኝ በፊት ያዘጃጁልንን የህያው ነቢያችን የሕልውነት ምስክርነታችሁን ያጠናክሩ።

ቁጥር አንድ በቤት ውስጥ የተመሰረቱ እና በቤተክርስቲያን የሚደገፉ መሆን።

ከሁለት አመት በፊት፣ ፕሬዘዳንት ራስል ኤም. ኔልሰን እንዳሉት፥ “‘ቤተክርስቲያን’ በመሰብሰቢያ ቤት የሚከሰት እና በቤት ውስጥ በሚከናወነው የሚታገዝ እንደሆነ ማሰብን ተለማምደናል። በዚህ ንድፍ ላይ ማስተካከያ ያስፈልገናል። … በቤት ውስጥ የተመሰረተ ቤተክርስቲያን፣ በሕንፃዎች ውስጥ በሚከናወነው በሚደገፈው።”12 እንዴት ያለ ትንቢታዊ ማስተካከያ ነው! በቤት ውስጥ የተመሰረ የወንጌል ትምህርት በጊዜያዊነት የመሰብሰቢያ ቤቶች ከመዝጋት ጋር ተያይዞ ተግባራዊ ተደርጓል። ምንም እንኳን ዓለም መደበኛ ወደሆነው ሲመለስ እና እኛም ወደ ቤተክርስቲያን ስንመለስ፣ በወረርሽኙ ወቅት የተገነቡ በቤት ውስጥ የተመሰረተ የወንጌል ጥናት እና የመማር ዘይቤዎችን ማቆየት እንፈልጋለን።

በጌታም በይበልጥ የመወደድ ሁለተኛው ምሳሌ በከፍተኛ እና በቅዱስ መንገድ ማገልገልነው።

ምስል
ማገልገል

በ2018 (እ.አ.አ)፣ ፕሬዘደንት ኔልሰን አገልግሎትን “እርስ በራስ [እንደምንከባከብበት] መንገድ” ማስተካከያ አስተዋወቁ።13 ወረርሽኙ የአገልጋይነት ክህሎታችንን ለማጎልበት በርካታ ዕድሎችን አስተዋውቋል። አገልጋይ ወንድሞች እና እህቶች፣ ወጣት ሴቶች እና ወጣት ወንዶች፣ እና ሌሎችም የጓሮ እንክብካቤን፣ ምግብን፣ መልዕክቶችን በቴክኖሎጂ በኩል፣ እና እርዳታ የሚያስፈልጋቸውን ለመባረክ የቅዱስ ቁርባን ስርዓትን ለማቅረብ እጃቸውን ዘርግተዋል። ቤተክርስቲያኗ ራሷም በወረርሽኙ ጊዜ ከዚህ በፊት ታይቶ በማይታወቅ ለምግብ ባንኮች፣ ለቤት አልባ መጠለያዎች፣ እና ለስደተኞች ድጋፍ ማዕከላት በማሰራጨት እና በዓለም ላይ በጣም አስከፊ ወደሆኑት የረሃብ ሁኔታዎች በሚመሩ ፕሮጀክቶች እያገለገለች ትገኛለች። የሴቶች መረዳጃ ማህበር እህቶች እና ቤተሰቦቻቸው በሚሊዮን የሚቆጠሩ የፊት ጭምብሎችን ለጤና እንክብካቤ ሰራተኞች የመስራትን ጥሪ ምላሽ ሰጡ።

ምስል
የበጎ አድራጎት ስራ
ምስል
ጭምብሎችን መስራት

በጣም የመባረክ ምሳሌም በቤተመቅደስ ስርዓቶች መመለስ ከፍተኛ ደስታን ማግኘት ነው።

ምስል
እህት ካይትሊን ፓልመር

ይህ በተሻለ በታሪክ ይገለጻል። እህት ኬትሊን ፓልመር ባለፈው ሚያዝያ የተልእኮ ጥሪዋን በተቀበለች ጊዜ፣ እንደ ሚስዮናዊነት በመጠራቷ በጣም ተደሰተች፤ ነገር ግን መንፈሳዊ ስጦታን ለመቀበል እና ቅዱስ ቃል ኪዳኖችን ለመቀበል ወደ ቤተመቅደስ መሄድ እኩል አስፈላጊ እና ልዩ እንደሆነ ተሰማት። መንፈሳዊ ስጦታዋን ለመቀበል ቀጠሮ ከተቀበለች ከአጭር ጊዜ በኋላ በአለም አቀፍ ወረርሽኝ ምክንያት ሁሉም ቤተመቅደሶች ለጊዜው እንደሚዘጉ ማስታወቂያው መጣ። ይህንን ልብ የሚነካ መረጃ ከተቀበለች በኋላ፣ በሚስዮን ማሰልጠኛ ቦታ ስልጣኔን የምታገኘው በይነመረብ እንደሆነ ተማረች። ለኬትሊን እነዚህ የሚያበሳጩ ሁኔታዎች ቢኖሩም፣ መንፈሷን ከፍ ለማድረግ ትኩረት ሰጥታለች።

ምስል
እህት ኬትሊን ፓልመር በቤት በሚገኝ የሚስዮን ማሰልጠኛ ቦታ

በመካከለኛ ወራቶች ውስጥ እህት ፓልመር በቤተመቅደስ የመገኘት ተስፋዋን በጭራሽ አላጣችም። ከመሄዷ በፊት ቤተመቅደሶች እንዲከፈቱ ቤተሰቦ ጾሙና ጸልዩ። ካይትሊን ብዙውን ጊዜ በቤት የሚስዮን ማሰልጠኛ ትምህርቷን የምትጀምረው፣ “ዛሬ ተአምር የምንቀበልበት እና ቤተመቅደሶች የሚከፈቱበት ቀን ይሆን?” በማለት ነው።

በነሐሴ 10 ቀን (እ.አ.አ) ቀዳም አመራር እርሷ ወደም ታገለግልበት ቦታ በአውሮፕላን በምትበርበት ጠዋት ማለዳ ቀን ላይ የካይትሊን ቤተመቅደስ የህያው ስነ ስርዓቶችን ለማከናወን እንደሚከፈት አስታወቁ። በቤተመቅደስ ተገኝታ በአውሮፕላኑ ለመብረር አትችልም ነበር። ለስኬት ብዙ ተስፋ ሳይኖራቸው፣ ቤተሰቧ የሚጸልዩት ተአምር እውን ሊሆን የሚችልበት መንገድ ካለ ለማየት የቤተመቅደሱን ፕሬዝዳንት ማይክል ቬሊንጋን አነጋገሩ። ጾማቸው እና ጸሎታቸው መልስ አገኙ!

ምስል
የፓልመር ቤተሰብ በቤተመቅደስ ውስጥ

አውሮፕላኑ ከመነሳቱ በፊት በለሊት 8 ሰዓት ላይ፣ እምባ የያዛቸውን እህት ፓልመር እና ቤተሰቧ በቤተመቅደስ በሮች ላይ ፈገግ ያሉ የቤተመቅደሱ ፕሬዘደንት በእንደዚህ ቃላት ሰላምቷ ሰጧቸው፣ “መልካም ጠዋት፣ የፓልመር ቤተሰብ፣ እንኳን ወደ ቤተመቅደስ በደህና መጣችሁ!” ወደ ቤተመቅደስ ኑ። የግል መንፈሳዊ ስጦታ ስርዓቷን እየፈጸመች እያለች፣ የሚቀጥለው ቤተሰብ በበሩ ላይ እየጠበቁ ስለሆነ በፍጥነት እንዲሄዱ ተጠየቁ። ወደ አውሮፕላን ማረፊያውም በቀጥታ ነድተው ወደ ትልዕኮዋ ለምትሄድበት በጊዜ እንድትደርስ አደረጉ።

ምስል
እህት ፓልመር በአውሮፕላን ማረፊያ ውስጥ

በዓለም ዙሪያ ያሉ ቤተመቅደሶች በየደረጃው እንደገና ሲከፈቱ በበርካታ ወራቶች ያመለጥናቸው የቤተመቅደስ ስርዓቶች ከዚህ በፊት ከገመቱት የበለጠ አስደሳች ይመስላሉ።

ስዘጋም፣ እባካችሁ የነቢዩ ጆሴፍ ስሚዝን አበረታች፣ ቀናተኛ፣ አነቃቂ ቃላትን አዳምጡ። በሕገ-ወጥ መንገድ ሊይዙት ከሚፈልጉት ሰዎች በመደበቅ በናቩ ውስጥ ታግዶ እና ተገድቦ በችግር እና በተናጥል እነሱን እንደጻፈ ማንም በጭራሽ አይገምተውም።

“አሁን፣ በተቀበልነው ወንጌል ውስጥ ምን እንሰማለን? የደስታ ድምፅ! የምህረት ድምፅ ከሰማይ፤ እና ከምድር ውስጥም የእውነትን ድምፅ፤ የምስራች ዜና ለሙታን፤ ከህያውና ከሙታን የደስታ ድምፅ፤ የታላቅ ደስታን የምስራች ነው።

“እኛስ … እንዲህ ያለውን ታላቅ ተልእኮ ላይ መሳተፍ አይኖርብንም? ወደኋላ ሳይሆን ወደፊት ሂዱ። ድፍረት… ወደ ላይ፣ ወደ ድል እንሂድ! ልባችሁ ትደሰት፣ እናም በጣም ተደሰቱ። ምድርም በድንገት ትዘምር።”14

ወንድሞች እና እህቶች፣ አንድ ቀን እያንዳንዳችሁ የተሰረዙትን ክስተቶች እና የተከሰተውን ሀዘን፣ ብስጭት እና የብቸኝነት አስተናጋጅ በበረከቶች ሲሸፈን እና በእምነት እና በምስክሮች ሲጨምር እነዚህን ለማየት ወደኋላ እንደምትመለከቱ አምናለሁ። በዚህ ሕይወት እና በሚመጣው ሕይወት መከራዎቻችሁ፣ አሞኒሀችሁ፣ የልበርቲ እስር ቤታችሁ፣ ለእርናንተ ጥቅም የተቀደሱ እንደሚሆኑ አምናለሁ።15 ከኔፊ ጋር፣ እኔም ጸልያለሁ፣ በጊዜያችን የመከራን መኖር እንድንገነዘብ፣ በተመሳሳይ ጊዜም በጌታ እጅግ የተወደድን እንደሆንን እንድንገነዘብ።

ለመከራ አዲስ ባልነበረው እናም አላቂ ባልሆነው የሀጢአት ክፍያው ከሁሉም ነገሮች በታች ሰለወረድው ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ በመመስክር እጨርሳለሁ።16 ሀዘናችንን፣ ህመማችንን እና ጥድፊያችንን እርሱ ይረዳል። እርሱ የእኛ አዳኝ፣ ቤዛችን፣ ተስፋችን፣ መጽናኛችን፣ እና ፈጻሚያችን ነው። ስለዚህ የምመሰክረው በእርሱ ቅዱስ ስም፣ በኢየሱስ ክርስቶስ ነው፣ አሜን።