አጠቃላይ ጉባኤ
ጌታን መጠበቅ
የጥቅምት 2020 (እ.አ.አ) አጠቃላይ ጉባኤ


ጌታን መጠበቅ

እምነት ማለት በመልካም እና በመጥፎ ጊዜ እግዚአብሔርን መታመን ማለት ነው፣ እንዲሁም ምንም እንኳን ያ እሱ ክንዱን ለእኛ ወክሎ ሲገለጥ እስክንመለከት ድረስ የተወሰነ መከራን መቀበል ቢያጠቃልልም።

ውድ ወንድሞቼ እና እህቶቼ፣ ሁላችንም—ከሁሉም በላይ እኔም—ከውድ ነቢያችን ፕሬዘደንት ራስል ኤም. ኔልሰን የመጨረሻን ንግግር ለማዳመጥ በጉጉት እንጠብቃለን። ይህም አስገራሚ ጉባኤ ነበር፣ ነገር ግን ለሁለተኛ ጊዜ ይህ ኮቪድ-19 በባህል በጉባኤ አዳራሽ ስር የምንሰበሰብበትን እንዳናደርግ አስገድዶናል። በዚህ ፀጉራችንን እየነቀለ በሚመስለው ተላላፊ ወረርሽኝ በጣም ተዳክመናል። እናም እንደሚታየው የተወሰኑ ወንድሞቻችን ያንን መንገድ የተከተሉ ይመስላል። በማንኛውም መንገድ ለተጠቁ ሰዎች በተለይም የሚወዱትን ላጡት ዘወት እንደምንጸልይ እባካችሁ እወቁ። ይህ እጅግ በጣም ለረጅም ጊዜ እየሄደ እንዳለ ሁሉም ይስማማል።

በእኛ ላይ ከሚደርስብን ችግር እፎይታን ለማግኘት እስከ መቼ እንጠብቃለን? እየጠበቅን አሁንም እየጠበቅን እና እርዳታ መምጣቱ በጣም ቀርፋፋ በሚመስልበት ጊዜ የግል ሙከራዎችን ስለመቋቋምስ? ሸክሞች ከምንሸከመው በላይ ሲመስሉ ለምን ይዘገያል?

እንደ እነዚህ ያሉ ጥያቄዎችን እየጠየቅን፣ ከሞከርን በዚያ አከባቢ ውስጥ ከተመዘገበው በጣም ቀዝቃዛው የክረምት ወቅት ከለዛዛ እና ከጨለማ እስር ቤት ውስጥ የሚያስተጋባ የሌላውን ጩኸት መስማት እንችላለን።

“እግዚአብሔር ሆይ፣ የት ነህ?” የሚለውን ከልብርቲ እስር ቤት ጥልቀት እንሰማለን። “እና የተሰወርክበትን ስፍራ የሚሸፍነው ድንኳን የት ነው? እጅህስ ለምን ያህል ጊዜ ይቆያል?”1 ለምን ያህል ጊዜ፣ ጌታ ሆይ፣ ለምን ያህል ጊዜ?

ስለዚህ እኛ ሀዘኖች ሲደክሙን ወይም በልባችን ውስጥ ያለው ህመም እየገፋ ሲሄድ፣ እንደዚህ ያሉ ጥያቄዎችን ለመጠየቅ የመጀመሪያ አይደለንም የመጨረሻም አንሆንም። አሁን የምናገረው ስለ ወረርሽኝ ወይም ስለ እስር ቤቶች ሳይሆን ማንኛውንም ዓይነት ፈተና ስለሚጋፈጡት ስለ እናንተ፣ ስለቤተሰባችሁ እና ስለ ጎረቤቶቻችሁ ነው። እኔ የምናገረው ማግባት ስለሚፈልጉ እና ስላላገቡት ወይም የተጋቡ ቢሆኑም ግንኙነታቸው ትንሽ ትንሽ ሰለስቲያላዊ እንዲሆን ጉግት ስላላቸው ነው። እኔ የምናገረው የማይፈለጉ ከባድ ህመም—ምናልባትም የማይድን ሊሆን የሚችል—ስለመጣባቸው ወይም መድኃኒት ከሌለው የዘረመል ጉድለት ጋር የዕድሜ ልክ ስቃይ ስለሚገጥማቸው ነው። እኔ የምናገረው በስሜታዊ እና የአእምሮ ጤንነት ችግሮች በነፍሳቸው ላይ ከበድ አድርጎት ስለሚሰቃዩት እና እነርሱን ስለሚወዱት እና አብረው ስለሚሰቃዩት ሰዎች ልብ ነው። እኔ የምናገረው አዳኙ ፈጽሞ እንዳንረሳ ስለነገረን ድሆች ነው፣ እናም የምናገረው ዕድሜው/ዋ ምንም ይሁን ምን፣ እርሱ/ሷ ከፀለይንበት መንገድ የተለየ መንገድ ስለመረጠ/ች ልጅ መመለስ ስለምትጠብቁትም ነው።

በተጨማሪም፣ በግል የምንጠብቅባቸው ይህ ረጅም ነገሮች ዝርዝር እንኳን በጋራ የሚገጠሙንን ትልቅ ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊ እና ማህበራዊ ጉዳዮችን ለመፍታት እንደማይሞክር እገነዘባለሁ። የሰማያዊው አባታችን በግልፅ የሚጠብቀን እነዚህን ግራ የሚያጋቡ የህዝብ ጉዳዮችን እንዲሁም የግል ጉዳዮችን እንድንፈታ ነው፣ ነገር ግን ያ ትልልቅ ዓለም አቀፍ ጉዳዮችን የተመለከተ ወይም አነስተኛ የግል ጉዳዮችን የሚመለከት ቢሆንም፣ በሕይወታችን ውስጥ የእኛ ምርጥ መንፈሳዊ ጥረት እና ልባዊ ጸሎቶች እንኳን የምንጓጓላቸውን ድሎች የማይሰጡበት ጊዜ ይኖራል። ስለዚህ አብረን ስንሰራ እና ለአንዳንዶቹ ጸሎቶቻችን መልስ ስንጠብቅ፣ እነርሱ እንደሚሰሙ እና ምናልባት በወቅቱ ወይም በፈለግነው መንገድ ባይሆንም እንደሚመለሱ የእኔን ሐዋርያዊ ቃል እሰጣችኋለሁ። ነገር ግን እነርሱ ሁል ጊዜ መልስ የሚሰጡበት ሁሉን አዋቂ እና ለዘለአለም ርህሩህ የሆነው ወላጅ በወቅቱ በሚሰጥበት መልስ ነው። የተወደዳችሁ ወንድሞቼ እና እህቶቼ፣ እባካችሁ የማይተኛና የማያንቀላፋው2 እርሱ መለኮታዊ ፍጡር ማድረግ ከሚገባው ሁሉ በላይ ለልጆቹ ደስታ እና የመጨረሻ ከፍ ከፍ መደረግ እንደሚያስብ ተገንዘቡ። እርሱም ንጹህ ፍቅር፣ ግርማዊነትን የሚያመሳስል ነው፣ እና ስሙም መሀሪ አባት ነው።

“እንደዚህ ከሆነ፣” እንዲህ ትሉ ይሆናል፣ “ፍቅሩ እና ርህራሄው የግል ቀይ ባህሮቻችንን በቀላሉ አይከፍልም እናም በደረቅ መሬት ላይ በችግሮቻችን ውስጥ እንድንጓዝ ሊያደርገን አይፈቅድምን? 21ኛው ክፍለ ዘመን የነበሩትን እጅግ አስደንጋጭ የጃርት ክራኮቻችንን ሁሉ ለመብላት የ21ኛው ክፍለ ዘመን የባህር ወፎችን አይልክልንምን?

ለእነዚህ ጥያቄዎች የሚሰጠው መልስም “አዎን፣ እግዚአብሔር ተአምራትን በቅጽበት ሊያቀርብ ይችላል፣ ነገር ግን ይዋል ይደር እንጂ የሟች ጉዞአችን ጊዜዎች እና ወቅቶች እሱ እና እሱ ብቻ የሚመሩ እንደሆኑ እንማራለን” የሚል ነው። ያንን የቀን መቁጠሪያ ለእያንዳንዳችን በተናጠል ያስተዳድራል። ወደ ቢታሴዳ ገንዳ ለመግባት ሲጠብቅ ወዲያውኑ ለተፈወሰው እያንዳንዱ ደካማ ሰው፣3 ሌላ ሰው ወደ ተስፋይቱ ምድር ለመግባት በመጠበቅ ለ40 ዓመታት በረሃ ውስጥ ያሳልፋል።4 በእምነታቸው ምክንያት በሚከበብ የእሳት ነበልባል በመለኮታዊ ጥበቃ ለተደረገላቸው ለእያንዳንዱ ኔፊ እና ሌሒ፣5 በሚነድደው የእሳት እንጨት ላይ የተቃጠለ አቢናዲ አለን።6 እናም በበኣል ካህናት ላይ ለመመስከር በቅጽበት ከሰማይ እሳት ከሰማይ ያወረደው ያም ኤልያስ፣7 ለዓመታት ዝናብ በማይኖርበት ጊዜ ታግሶ፣ ለተወሰነ ጊዜ በቁራ ጥፍር ውስጥ ሊሸከም የሚችል ረቂቅ ምግብ ብቻ የሚመግበው ያው ኤልያስ መሆኑን እናስታውሳለን።8 በእኔ ግምት ያ “ደስተኛ ምግብ” የምንለው ነገር ሊሆን አይችልም።

ነጥቡም? ነጥቡ ግን እምነት ማለት በመልካም እና በመጥፎ ጊዜ እግዚአብሔርን መታመን ማለት ነው፣ እንዲሁም ምንም እንኳን ያ እሱ ክንዱን ለእኛ ወክሎ ሲገለጥ እስክንመለከት ድረስ የተወሰነ መከራን መቀበል ቢያጠቃልልም።9 ብዙዎች በሕይወት ውስጥ የሚበጀው መልካም ነገር ሁሉንም መከራዎች ማስወገድ ነው፣ ማንም በጭራሽ በምንም ነገር ላይ መጨነቅ የለበትም በማለት በሚያምነው በእኛ ዘመናዊው ዓለም ውስጥ ይህ አስቸጋሪ ሊሆን ይችላል።10 ነገር ግን ያም እምነት በምንም ወደ “ክርስቶስም ሙላቱ”11አይመራንም።

ሽማግሌ ኔል ኤ. ማክስዌል በአንድ ወቅት የተናገሩትን አንድ ነገር ለማሻሻል እና ለማራዘም በመጣሬ ይቅርታ በመጠየቅ፣ እኔም “የአንድ ሰው ሕይወት … በእምነት የተሞላ እና ከጭንቀት ነፃ ሊሆን አይችልም” የሚል ሀሳብ አቀርባለሁ። ሌላ የሎሚ መጠጥ በብርጭቆ እየጠጣን በቀላሉ “በሕይወት ውስጥ በሞኝነት በመንሸራተት” እንዲህ ማለቱ አይሠራም፥ “ጌታ ሆይ፣ በጣም ጥሩ የሆኑ በጎነቶችህን ሁሉ ስጠኝ፣ ግን ሀዘን፣ ስቃይ፣ ህመም ወይም ተቃውሞ እንደማይሰጠኝ እርግጠኛ ሁን። እባክህ ማንም እንዳይወደኝ ወይም እኔን አሳልፎ እንዳይሰጥ፣ እና ከሁሉም በላይ በአንተ ወይም በምወዳቸው ሰዎች እንደተተውኩኝ በጭራሽ እንዳይሰማኝ አትፍቀድ። በእርግጥም፣ ጌታ ሆይ፣ መለኮታዊ ካደረጉህ ልምዶች ሁሉ እንድርቅ ጥንቃቄ አድርግልኝ። እናም በእያንዳንዱ የተጫጫነው ሸርተቴ ሲያልቅ፣ በምቾት ክርስቲያንነት ደመናዬ ላይ ስንሳፈፍ ምን ያህል ጥንካሬያችንና ባህሪያችን ከአንተ ጋር እንደሚመሳሰል በመመካት፣ መጥቼ ከአንተ ጋር እኖር ዘንድ እባክህ ፍቀድልኝ።”12

የተወደዳችሁ ወንድሞቼ እና እህቶቼ፣ ክርስትያንነት የሚያጽናና ቢሆንም ብዙ ጊዜ ምቾት አይሰጥም። እዚህ እና ከዚህ በኋላ ወደ ሚገኘው ቅድስና እና ደስታ የሚወስደው መንገድ ረዥም እና አንዳንዴም ድንጋያማ ነው። እሱን ለመራመድ ጊዜ እና ጽናት ይጠይቃል። ነገር ግን በእርግጥም እንዲህ ማድረጋችን ትልቅ ዋጋ ያለው ነው። ይህም እውነት በግልፅ እና በሚያስተማምን ሁኔታ አልማ ምዕራፍ 32 ያስተምራል። በዚያም ታላቁ ሊቀ ካህን የእግዚአብሔር ቃል በልባችን እንደ ቀላል ዘር ከተተከለ፣ እና እርሱን ውሀ ለመስጠት፣ ለመንከባከብ፣ ለማረም፣ ለመመገብ፣ እና ለማበረታታት በቂ እንክብካቤ ካደረግን፣ ይህም በወደፊት “የተከበረውን፣ ከጣፋጮች ሁሉ ጣፋጭ የሆነውን፣” የዚህ መበላት ከእንግዲህ ጥማት እና ረሃብ ወደሌለበት ሁኔታ የሚመራ ፍሬን ያሳድጋል።13

በዚህ አስደናቂ ምዕራፍ ውስጥ ብዙ ትምህርቶች ተምረዋል፣ ነገር ግን ከሁሉም ዋናው አነጋገር ቢኖር ዘሩ “ለእዚያ ፍሬ በእምነት ዓይንበመጠበቅ ” መመገብ እንዳለበት እና እስኪበስል ድረስ መጠበቅ እንዳለበት ነው።14 አልማ እንዳለው፣ አዝመራችን “ከጊዜ በኋላ” ይመጣል።15 ይህን የሚያስገርም መመሪያውን በትጋት እና በትዕግስት የእግዚአብሔርን ቃል በልባችን ውስጥ በመንከባከብ፣ እርሱ እንደሚለው “ዛፉ ፍሬ እንዲያስገኝላችሁ” ድረስ በታጋሽነት“መጠበቅ”እንዳለብን ለሶስት ጊዜ መደጋገሙ የሚያስገርም አይደለም።16

ኮቪድ እና ነቀርሳ፣ ጥርጣሬ እና ተስፋ መቁረጥ፣ የገንዘብ ችግር እና የቤተሰብ ፈተናዎች። እነዚህ ሸከሞች መቼ ይነሳሉ? መልሱም “ከጊዜ በኋላ” ነው።17 እናም ያ አጭር ጊዜም ሆነ ረዥም እኛ ሁልጊዜ የምንወስነው አይደለም፣ ነገር ግን በእግዚአብሔር ጸጋ፣ የኢየሱስ ክርስቶስን ወንጌል በጥብቅ ለያዙት በረከቶቹ ለእነሱ ይሆናሉ። ይህ ጉዳይ ከረጅም ጊዜ በፊት በጣም የግል በሆነ የአትክልት ስፍራ እና በኢየሩሳሌም በሚገኘው በጣም ሕዝባዊ ኮረብታ ላይ ተፈትቷል።

አሁን ውድ ነቢያችን ይህንን ጉባኤ የሚዘጉበትን ይህን በማስታወስ እናዳምጥ፣ ልክ ራስል ኔልሰን በህይወታቸው በሙሉ እንዳሳዩት፣ “ጌታን የሚጠብቁ ኃይላቸውን ያድሳሉ [እናም] ንስር ክንፍ ላይ ይወጣሉ፤ ይሮጣሉ አይታክቱም፤ … ይሄዳሉ አይደክሙም።”18 “ከጊዜ በኋላ”፣ አሁንም ይሁን በኋላ፣ እነዚያ በረከቶች ከሀዘን እረፍት እና ከስቃይ ነጻነት ለማግኘት ለምትሹት ለሁላችሁም እንዲመጡ እጸልያለሁ። ስለእግዚአብሔር ፍቅር እና በሕይወት ውስጥ ለሚያጋጥሙን ጉዳዮች ሁሉ በዚህም ሆነ በዛ መልስ ስለሆነው ስለእርሱ ግርማዊ ወንጌል በዳግም መመለስ ምስክር እሰጣለሁ። በመሐሪው ኢየሱስ ክርስቶስ ስም፣ አሜን።