ምዕራፍ ፬
ንጉስ ቢንያም ንግግሩን ቀጠለ—ደህንነት የሚመጣው በኃጢያት ክፍያው አማካኝነት ነው—ለመዳን በእግዚአብሔር እመኑ—የኃጢአታችሁን ስርየት በእምነታችሁ አግኙ—ያላችሁን ነገር ለድሆች አካፍሉ—ሁሉንም ነገር በጥበብና በስርዓት አድርጉ። ፻፳፬ ም.ዓ. ገደማ።
፩ እናም አሁን፣ እንዲህ ሆነ ንጉስ ቢንያም በጌታ መልአክ የተሰጠውን ቃላት ተናግሮ ሲጨርስ፣ ዙሪያ ገባውን ተመልክቶ ዐይኑን በህዝቡ ላይ አሳረፈ፣ እናም የጌታ ሀፍርሃት በእነርሱ ላይ በመምጣቱ የተነሳ በመሬት ላይ ወድቀው ተመለከታቸው።
፪ እናም ሀበስጋቸው እራሳቸውን ከመሬት ትቢያ እንኳን ለአሳንሰው ተመለከቱ። እናም ሁሉም በአንድ ድምፅ እንዲህ ብለው ጮሁ፥ አቤቱ ምህረትን ስጠን፣ እናም ለኃጢአታችን ይቅርታን እናገኝ ዘንድና ልባችን ንፁህ ይሆን ዘንድ የክርስቶስን የደም ሐክፍያ በእኛ ላይ አድርግ፤ ሰማይና ምድርን እንዲሁም ሁሉንም ነገሮች መበፈጠረው በሰው ልጆች መካከል በሚመጣው በእግዚአብሔር ልጅ በክርስቶስ ኢየሱስ እናምናለንና።
፫ እናም እንዲህ ሆነ እነዚህን ቃላት ከተናገሩ በኋላ የጌታ መንፈስ በእነርሱ ላይ መጣ፤ እና ንጉስ ቢንያም በተናገረው ቃላት መሰረት በሚመጣው በኢየሱስ ክርስቶስ ባላቸው ታላቅ ሀእምነት የተነሳ፣ ለኃጢአታቸውም ለስርየትን በመቀበል፣ እናም ሐየህሊና ሰላምም በማግኘት በደስታ ተሞልተው ነበር።
፬ እናም ንጉስ ቢንያም በድጋሚ አፉን ከፍቶ እንዲህ ሲል መናገር ጀመረ፥ ጓደኞቼና ወንድሞቼ፣ ወገኖቼና ህዝቤ ለእናንተ የምናገረውን ቀሪውን ቃሌን ታደምጡኝ እናም ትረዱኝ ዘንድ በድጋሚ ትኩረታችሁን እፈልጋለሁ።
፭ እነሆም በዚህ ጊዜ ሀየእግዚአብሔርን ቸርነት ማወቅ እናንተ ምንም እንዳልሆናችሁ፣ እናም እንደማትረቡና እንደውድቀታችሁ ሁኔታ ስሜት የሚያነቃችሁ ከሆነ—
፮ እንዲህ እላችኋለሁ፣ የእግዚአብሔርን ቸርነት እናም ወደር የሌለውን ሀይሉንና፣ ጥበቡን፣ እንዲሁም ረዥም ፅናትና፣ እናም ለሰው ልጆች ያለውን ታጋሽነቱን፣ ደግሞም ሀእምነቱን በጌታ ላይ ያሳረፈና፣ ትዕዛዛቱን ለመጠበቅ ትጉህ ለሆነው፣ እና እስከህይወቱ፣ ይህም ማለቴ የስጋ ሰውነት ህይወቱ መጨረሻ ድረስ በእምነት ለጸናው ደህንነት እንዲመጣለት ዘንድ፣ ለከዓለም መፈጠር ጀምሮ የተዘጋጀውን ሐየኃጢያት ክፍያ መወደማወቅ ከመጣችሁ—
፯ ይህ አይነቱ ሰው ከዓለም መፈጠር ጀምሮ፣ ከአዳም ሀውድቀት በኋላ ለነበሩት፣ ወይም ለአሉት፣ ወይም እስከ አለም መጨረሻ ድረስ ስለሚኖሩት፣ ለሰው ልጆች ሁሉ በተዘጋጀው የኃጢያት ክፍያ ደህንነትን ይቀበላል እላለሁ።
፰ እናም ደህንነት የሚገኝበት መንገድ ይህ ነው። እናም ከዚህ ከተነገረው በስተቀር ሌላ ደህንነት ሀየለም፤ እኔ ከተናገርኳችሁ ሁኔታ በቀር ሰዎች የሚድኑበት ሌላ መንገድ የለም።
፱ በእግዚአብሔር እመኑ፤ እርሱ እንዳለ፣ እናም እርሱ በሰማይም በምድርም ያሉትን ሁሉንም ነገሮች እንደፈጠረ እመኑ፤ በሰማይና በምድር ሁሉ ሀጥበብና ሀይል እንዳለው እመኑ፤ ጌታ ሊረዳቸው የሚችለውን ነገሮች ሁሉ ሰው ለእንደማይረዳቸው እመኑ።
፲ እናም እንደገና፤ ለኃጢአታችሁ ሀንስሃ መግባትና፣ መተው፣ እንዲሁም በእግዚአብሔር ፊት ትሁት መሆን እንዳለባችሁ እመኑ፤ ለይቅር እንድትባሉ ከልባችሁም ጠይቁ፤ እናም አሁን፣ እነዚህን ነገሮች ሁሉ ሐካመናችሁ መመፈፀማችሁን አረጋግጡ።
፲፩ እናም እንደገና በፊት እንደተናገርኳችሁ እናገራችኋለሁ፣ የእግዚአብሔርን ክብር ለማወቅ የምትመጡ ከሆነ፣ እንዲሁም ቸርነቱንና ታጋሽነቱን ካወቃችሁና ፍቅሩን ሀከቀመሳችሁ፣ ነፍሳችሁ እጅግ እንድትደሰት የሚያደርገውን ለኃጢአታችሁ ለስርየትን ከተቀበላችሁም፣ የእግዚአብሔርን ታላቅነትና የራሳችሁን ሐከንቱነት፣ ወደ እናንተ የማትረቡ ፍጥረት ያለውን የእርሱን መጥሩነትና ትዕግስት፣ እናም የጌታንም ስም ቀን በቀን ሠበመጥራትና በመልአኩ አፍ በተነገረለት ወደፊት በሚመጣው እምነት አፅንታችሁ በመቆም በጥልቅ ረትህትና እንኳን ራሳችሁን እንድታዋርዱ እንድታስታውሱትና ሁልጊዜም በማስታወስ እንድትይዙት እፈልጋለሁ።
፲፪ እናም እነሆ፣ እላችኋለሁ ይህንን የምታደርጉ ከሆነ ሁልጊዜ ትደሰታላችሁ፣ በእግዚአብሔር ሀፍቅር ትሞላላችሁም፣ ሁልጊዜ የኃጢአታችሁን ስርየት ለታገኛላችሁም፤ እናም እናንተን በፈጠረው ክብር እውቀት፣ ወይንም ትክክለኛና እውነተኛ በሆነው እውቀት ታድጋላችሁ።
፲፫ እናም ሀበሰላም ለመኖርና፣ ለእያንዳንዱ ሰው የሚገባውን ለመስጠት እንጂ፣ እርስ በርሳችሁ የመጎዳዳት ሃሳብ አይኖርባችሁም።
፲፬ እናም ሀልጆቻችሁ ተርበው አለበለዚያም ተራቁተው እንዲሄዱ አትፈቅዱም፤ የእግዚአብሔርንም ህግ እንዲተላለፉ፣ እርስ በርሳቸውም ለእንዲጣሉ እናም በአባቶቻችን ክፉ መንፈስ ተብሎ የተነገረለትን የፅድቅ ሁሉ ጠላት የሆነውንና የኃጢያት አለቃ የሆነውን ዲያብሎስን እንዲያገለግሉ አትፈቅዱም።
፲፭ ነገር ግን በእውነትና በጥሞና መንገድ ሀእንዲራመዱ ለታስተምሯቸዋላችሁ፣ እርስ በርሳቸው ሐእንዲዋደዱ እንዲሁም አንደኛው ሌላኛውን እንዲያገለግል ታስተምሯቸዋላችሁ።
፲፮ እናም ደግሞ፣ እናንተ ራሳችሁ የእናንተን ሀእርዳታ ፍለጋ የቆሙትን ትረዷቸዋላችሁ፤ ፍላጎት ላላቸው ቁሳቁሳችሁን ትሰጧቸዋላችሁ፤ እናም ለለማኙም እናንተን የሚለምነው በከንቱ እንዲሆንና፣ እንዲጠፋ ማስወጣትን አትፈቅዱም።
፲፯ ምናልባት እንዲህ ሀትላላችሁ፥ ይህ ሰው ስቃይን በራሱ ላይ አምጥቷል፣ ስለሆነም እጄን እሰበስባለሁ፣ እናም እንዳይቸገር ከእንጀራዬም ሆነ ከአለኝ ነገር አልሰጠውም ምክንያቱም ቅጣቶቹ ትክክል ናቸውና—
፲፰ ነገር ግን እላችኋለሁ፣ ሰው ሆይ፣ ማንም ይህንን ያደረገ ንስሃ ለመግባት ታላቅ ምክንያት ይኖረዋል፤ እናም በፈፀመው ነገር ንስሃ ካልገባ በስተቀር ለዘለዓለም ይጠፋል፣ እናም በእግዚአብሔር መንግስት ቦታ አይኖረውም።
፲፱ እነሆም ሁላችንስ ለማኞች አይደለንምን? ሁላችንም ባሉን ቁሳቁሶች ሁሉ፣ በምግብና በልብስ፣ እንዲሁም በወርቅና፣ በብር፣ እናም ከሁሉም አይነት ባሉን ሀብቶች በአንዱስ ፍጡር፣ እንዲሁም በእግዚአብሔር ጥገኞች አይደለንምን?
፳ እናም እነሆ፣ በዚህ ጊዜም እንኳን ቢሆን፣ ስሙን ጠርታችኋልም፣ ለኃጢአታችሁ ስርየትን ለምናችኋልም። እናም በከንቱ እንድትለምኑ ፈቅዷልን? አይደለም፤ መንፈሱን በላያችሁ ላይ አፍስሷል፤ እናም ልባችሁ ሀበደስታ እንዲሞላ አድርጓል፣ እንዲሁም ስለዚህ ደስታችሁም እጅግ ታላቅ ሆኖ፣ መናገርም እንዳትችሉ አንደበታችሁን እንዲዘጋ አድርጓል።
፳፩ እናም አሁን፣ ለህይወታችሁና ላላችሁና ለሆናችሁት ሁሉ የምትመኩበት እናንተን የፈጠረው እግዚአብሔር ትክክለኛ የሆነውን ማንኛውንም ነገር በእምነት፣ አገኛለሁ በማለት አምናችሁ የምትጠይቁትን ከሰጣችሁ፣ አቤቱ ያላችሁን ነገሮች አንዳችሁ ለሌላኛችሁ እንዴት ሀመካፈል ይገባችኋል።
፳፪ እናም አንድ ሰው እንዳይጠፋ ካላችሁ ሀብት እንድታካፍሉት የሚጠይቃችሁን ሀከፈረዳችሁበት፣ ከኮነናችሁት፣ የእናንተ ሳይሆን ህይወታችሁም እንኳን የእርሱ የሆነው የእግዚአብሔር የሆነውን ሀብታችሁን ለበመያዛችሁ ኩነኔያችሁም ምን ያህል ትክክል ይሆናል፤ ነገር ግን፣ ለሰራችኋቸው ነገሮችም ንሰሃን እናም ልመናን አላቀረባችሁም።
፳፫ እላችኋለሁ፣ ለዚህ ሰው ወዮለት ያለው ነገር ከእርሱ ጋር ይጠፋልና፣ እናም አሁን፣ የዚህን ዓለም ነገሮች ለአሉአቸው ሀባለጠጋዎች እነዚህን ነገሮች እናገራለሁ።
፳፬ እናም እንደገና ባይኖራቸውም፣ ግን በህይወት እንዲቆዩ በመጠኑም ለሚኖራቸው ድሆች እንደገና እንዲህ እላለሁ፤ ማለቴም እናንተ ስለሌላችሁ ለድሆች ለማትሰጡት ነው፤ በልባችሁ ስለሌለኝ አይደለም የማልሰጠው፣ ነገር ግን ቢኖረኝ ኖሮ ሀእሰጥ ነበር እንድትሉ እፈልጋለሁ።
፳፭ እናም አሁን፣ ይህንን በልባችሁ የምትሉ ከሆነ ከበደል የነፃችሁ ትሆናላችሁ፣ አለበለዚያ ግን ሀትኮነናላችሁ፣ እናም ኩነኔአችሁ የእናንተ ያልሆነውን በመመኘታችሁ ትክክል ነው።
፳፮ እናም አሁን፣ ለእናንተ ለተናገርኳቸው ለእነዚህ ነገሮች ሲባል—ይህም ማለት በእግዚአብሔር ፊት ከበደል ነፅታችሁ ሀትራመዱ ዘንድ ከቀን ወደ ቀን ለኃጢአታችሁ ስርየትን እንድታገኙ—የራሳችሁን ነገር ለለድሃ ሐእንድትሰጡ፣ እያንዳንዱ ሰው ባለው መጠን፣ የተራቡትን መበመመገብ፣ የታረዙትን በማልበስ፣ የታመሙትን በመጎብኘት እናም እንደፍላጎታቸው ለነፍሳቸውም ሆነ ለስጋቸው ደህንነት በቂ እርዳታን እንድትለግሱ እፈልጋለሁ።
፳፯ እናም እነዚህ ነገሮች ሁሉ በጥበብና በዕቅድ እንደተደረጉ ተመልከቱ፣ ሰው ከአቅሙ በላይ ሀፈጥኖ መሮጡ አስፈላጊ አይደለምና። እናም እንደገና፣ ሽልማቱን ያሸንፍ ዘንድ ትጉህ መሆኑ አስፈላጊ ነው፣ ስለዚህ፣ ሁሉም ነገሮች በስርዓት መደረግ አለባቸው።
፳፰ እናም ማንም ከእናንተ መካከል ከጎረቤቱ የተበደረ የተበደረውን ነገር በስምምነቱ መሰረት መመለስ እንዳለበት እንድታስታውሱ እፈልጋለሁ፣ አለበለዚያ ኃጢያትን ትፈፅማላችሁ፤ እናም ምናልባት ጎረቤቶቻችሁንም ደግሞ ኃጢያት እንዲፈፅሙ ታደርጋላችሁ።
፳፱ እናም በመጨረሻም፣ ኃጢያት ልትፈፅሙ የምትችሉባቸውን ነገሮች ሁሉ ልነግራችሁ አልችልም፤ ምክንያቱን መቁጠር የማልችለው ብዙ መንገዶችና ዘዴዎች ስለሚኖሩ ነው።
፴ ነገር ግን ይህን ያህል ልነግራችሁ እችላለሁ፣ ራሳችሁን፣ ሀሀሳባችሁንና፣ ለቃላችሁን፣ እናም ድርጊታችሁን የማታስተውሉና፣ የእግዚአብሔርን ትዕዛዝ ሐየማትጠብቁ፣ እናም የሚመጣውን ጌታችንን በተመለከተ የሰማችሁትን እስከ ህይወታችሁ መጨረሻ በእምነት የማትቀጥሉ ከሆናችሁ፣ መጥፋት ይገባችኋል። እናም አሁን፣ ሰው ሆይ፣ አስታውስ፣ እናም አትጥፋ።