ምዕራፍ ፳
ጌታ ዓላማውን ለእስራኤል ገለጠ—እስራኤልም በመከራ እቶን ተመረጠች፣ እናም ከባቢሎን ትወጣለች—ኢሳይያስ ፵፰ን አነጻፅሩ። ከ፭፻፹፰–፭፻፸ ም.ዓ. ገደማ።
፩ እናንተ በእስራኤል ስም የተጠራችሁ እናንተ ከይሁዳ ውኃ ይሁን ሀከጥምቀት ውኃ የወጣችሁ፣ በጌታ ስም የምትምሉ፣ በእውነት ሳይሆን፣ በፅድቅ ሳይሆን የእስራኤልን አምላክ የምትጠሩ የያዕቆብ ቤት ሆይ ይህን ስሙ እናም አድምጡ።
፪ ይሁን እንጂ ሀበቅድስት ከተማ ስም እራሳቸውን ይጠራሉ፣ ነገር ግን የሰራዊት ጌታ በሆነው በእስራኤል አምላክ ላይ ለአይደገፉም፤ አዎን፣ የሰራዊት ጌታ የእርሱ ስም ነው።
፫ እነሆ ሀየቀድሞውን ነገሮች ከጥንት ጀምሮ ተናግሬአለሁ፤ ከአፌም ወጥተዋል፣ አሳይቼአቸዋለሁ። በድንገትም አሳየኋቸው።
፬ እናም ይህንን ያደረግሁት ሀአንተ እልከኛ፣ አንገትህም የብረት ጅማት፣ ግንባርህም ናስ እንደሆነ ስለማውቅ ነው፤
፭ እናም ሀጣኦቴ ይህን አድርጓል፣ የተቀረፀው ምስሌ፣ ቀልጦ የተሰራው ምስሌ እነዚህን አዘዘኝ እንዳትል ፈርቼ አስቀድሜ ነግሬህ ነበር፤ ሳይሆንም አስተምሬህ ነበር።
፮ ይህን ሁሉ ተመልክተሀልና ሰምተሀል፤ እናም አንተ አትናገራቸውምን? አዲስ ነገሮች፣ እንዲሁም የተደበቁትንም ነገሮች፣ ከዚህ ጀምሮ አሳይቼህ ነበር፣ እና አንተ አላወቅሀቸውም።
፯ እነርሱም አሁን እንጂ ከጥንት ጀምሮ አልተፈጠሩም፣ አንተም እነሆ፥ አውቄአቸዋለሁ እንዳትል ስለእነዚህ ከመስማትህ በፊት ለአንተ ተገልጠውልህ ነበር።
፰ አዎን እናም አልሰማህም፣ አዎን አላወቅህም፤ አዎን ጆሮህም በዚያን ጊዜ አልተከፈተም፣ ምክንያቱም አንተ ፈፅሞ ሀወንጀለኛ እንደሆንክ ከማህፀንም ጀምሮ ህግን ተላላፊ ተብለህ እንደተጠራህ አውቃለሁና።
፱ ይሁን እንጂ ሀስለስሜ ቁጣዬን አዘገያለሁ፣ ስለምስጋናዬም ስል እንዳላጠፋህ ዘንድ እለይሃለሁ።
፲ ምክንያቱም እነሆ አንጥሬሀለሁ፣ ሀበመከራም እቶን መርጬሀለሁ።
፲፩ ስለእኔ አዎን ስለራሴ ይህን አደርገዋለሁ፣ ምክንያቱም ሀስሜ እንዲነቀፍ አልፈቅድም፣ እናም ክብሬንም ለሌላ ለአልሰጥም።
፲፪ ያዕቆብ ሆይ፣ የጠራሁህም እስራኤል ሆይ ስሙኝ፣ ምክንያቱም እኔ ነኝና፤ እኔ ሀየፊተኛው እናም ደግሞ እኔ መጨረሻው ነኝ።
፲፫ እጄም ደግሞ የምድርን መሰረት ሀመስርታለች፣ ቀኝ እጄም ሰማያትን ዘርግታለች። ጠራኋቸው እናም በአንድ ላይ ቆሙ።
፲፬ እናንተ ሁሉ በአንድ ላይ ተሰብስባችሁ አድምጡ፤ ከእነርሱ እነዚህን ነገሮች ያወጀላቸው ማን ነው? ጌታ እርሱንም ወድዶታል፤ አዎን እርሱም በእነርሱ የተናገረውን ሀቃል ይፈፅማል፣ እርሱም እንደሚያስደስተው ለበባቢሎን ላይ ያደርጋል፣ ክንዱም በከለዳውያን ላይ ይሆናል።
፲፭ ደግሞም ጌታ እንዲህ ይላል፤ እኔ ጌታ አዎን እኔ ተናገርኩ፤ አዎን እርሱን እንዲያውጅ ጠራሁት፣ አምጥቼውማለሁ፣ መንገዱንም ቀና ያደርጋል።
፲፮ ወደ እኔ ቅረቡ፣ እኔ ሀበስውር አልተናገርኩም፤ ከጥንት ጀምሮ፣ ከታወጀበት ጊዜ አንስቶ እኔ ተናገርኩ፣ እናም ጌታ እግዚአብሔርና መንፈሱ ልከውኛል።
፲፯ እናም ሀመዳኒትህ፣ የእስራኤል ቅዱስ ጌታ እንዲህ ይላል፤ የሚረባህን ነገር የማስተምርህ፣ በምትሄድበትም መንገድ ለየሚመራህ እኔ ጌታህ እግዚአብሔር ልኬዋለሁ።
፲፰ አቤቱ ሀትዕዛዛቴን ብትሰማ ኖሮ ሰላምህ እንደወንዝ፣ ፅድቅህም እንደባህር ሞገድ ይሆን ነበር።
፲፱ ሀዘርህም ደግሞ እንደ አሸዋ በሆነ ነበር፤ የሆድህም ትውልድ እንደባህር ጠጠር በሆነ ነበር፤ ስሙም ከፊቴ ባልጠፋ ወይም ባልፈረሰ ነበር።
፳ ከባቢሎን ሀውጡ፣ ከከለዳውያንም ኮብልሉ፣ በእልልታ ድምፅ ተናገሩ፣ ይህንም ተናገሩ እስከምድር ዳርቻ ድረስ አውሩ፤ ጌታ ለባርያውን ያዕቆብን ታድጎታል በሉ።
፳፩ እናም ሀአልተጠሙም ነበር፤ በበረሃ ውስጥ መራቸው፤ ውሃውንም ለከዓለቱ ውስጥ አፈለቀላቸው፤ ዓለቱንም ደግሞ ሰነጠቀውና ውኃው ፈለቀ።
፳፪ እናም ይህንን ሁሉና፣ ደግሞ ታላቅ ነገር ቢያደርግም፣ ለክፉዎች ሀሰላም የላቸውም ይላል ጌታ።