2010–2019 (እ.አ.አ)
ሁለተኛይቱ ታላቅ ትእዛዝ
የጥቅምት 2019 (እ.አ.አ) አጠቃላይ ጉባኤ


ሁለተኛይቱ ታላቅ ትእዛዝ

የእኛ ታላቁ ደስታ የሚመጣው ወንድሞቻችንን እና እህቶቻችንን ስንረዳ ነው።

ውድ ወንድሞቼ እና እህቶቼ በመጋራጃው በሁለቱም በኩል እስራኤልን ለመሰብሰብ ፣ ቤተሰቦቻችሁን ለማጠንከር እና እርዳታ የሚያስፈልጋቸውን ለመባረክ ለምታደርጉት ሁሉ አመሰግናለሁ። እንደ እውነተኛ የኢየሱስ ክርስቶስ ተከታዮች እየኖራችሁ ስለሆነም አመሰግናለሁ።1 ሁለቱን ታላቅ ትዕዛዛትን ታውቃላችሁ እግዚአብሔርን እና ባለንጀሮቻችሁን መውደድን። 2

ባለፉት ስድስት ወራቶች ውስጥ እህት ኔልሰን እና እኔ ወደ ማዕከላዊ እና ደቡብ አሜሪካ፣ የፓስፊክ ደሴቶችን እና በአሜሪካ ዉስጥ የተለያዩ ከተሞች ከሚገኙ በሺዎች ከሚቆጠሩ ቅዱሳን ጋር ተገናኝተን ነበር። ስንጓዝ ተስፋችን የእናንተንእምነት ለመገንባት ነው። ሁልጌዜ የምንመለሰው ባገኘናቸው አባላትና ጓደኞች የእኛ እምነት ተጠናክሮ ነው። በቅርቡ ካጋጠሙን ትርጉም ከነበራቸው ጊዚያት መካከል ሶስቱን ላካፍላችሁ?

ምስል
ፕሬዘዳንት ኔልሰን በኒውዘርላንድ ውስጥ
ምስል
ፕሬዘዳንት ኔልሰን በኒውዘርላንድ ውስጥ

ግንቦት ላይ እህት ኔልሰን እና እኔ ከሽማግሌ ጌረት ደብሊው. እና ከእህት ሱዛን ጎንግ ጋር ወደ ደቡብ ፓስፊክ ተጉዘን ነበር። ኦክላንድ ኒውዚላንድ በነበርን ጊዜ ከሁለት ወር አስቀድሞ ንጹሃን አምላኪዎች በአሰቃቂ አመጻ በጥይት የተገደሉበት የሁለት መስጊድ ኢማሞች ጋር በክርስቶስ ቤተክርስትያን ኒውዚላንድ የመገናኘት ክብር አግኝተን ነበር።

ከሌላ እምነት ለሆኑትን ለእነዚህ ወንድሞቻችን የተሰማንን ሃዘን እናም ለሃይማኖት ነጻነት ያለንን የጋራ አቋማችንን አረጋገጥን።

በተጨማሪም መስጊዱን እንደገና ለማስገንባት የጉልበት እና መጠነኛ የገንዘብ ድጋፍ አድርገን ነበር። ከእነዚህ የእስልምና መሪዎች ጋር የነበረን ስብሰባ በወንድማዊነት ደግነት የተሞላ ነበር።

ምስል
ተሸከርካሪ ወንበር ተቀባይ በአርጀንቲና
ምስል
ተሸከርካሪ ወንበር ተቀባይ በአርጀንቲና

ነሓሴ ላይ ከሽማግሌ ክዊንተን ኤል. እና ከእህት ሜሪ ኩክ ጋር እህት ኔልሰን እና እኔ በቦኑስ አይረስ —አብዛኛዎቹ ከኛ እምነት ካልሆኑት —በኋላኛው ቀን ቅዱሳን በጎ አድራጎት በተለገሰ ዊልቼር ህይወታቸው ከተቀየረላቸው ሰዎች ጋር ተገናኝተን ነበር፣ አዲስ ላገኙት መንቀሳቀሻ ደስታ የተሞላ ምስጋናቸውን ሲያቀርቡ ልባችን ተነሳስቶ ነበር።

ሶስተኛው የከበረ ጊዚያችን የተከሰተው ከጥቂት ሳምንታት በፊት በሶልት ሌክ ከተማ ነው። ያም የመጣው በልደት ቀኔ ሜሪ ብዬ ከምጠራት —የ14 አመት ታዳጊ ሴት ከተቀበልኩት ልዩ ደብዳቤ ነበር።

ሜሪ እኔ እና እሷ ስላለን ተመሳሳይ ነገር ጻፈች።እኛ 10 ልጆች አሉን። እኛ 10 ልጆች አሉን። መንደሪኛ ትናገራለህ። እኔን ጨምሮ በቤተሰባችን ዉስጥ ሰባታችን ጉዲፈቻ የሆንነው ከቻይና ነው ስለዚህ ማንዳሪን የመጀመርያ ቋንቋችን ነው። አንተ የልብ ቀዶ ህክምና ሃኪም ነህ። እህቴ ሁለት የልብ [ቀዶ ህክምና] አድርጋለች። አንተ የሁለት ሰዓት የቤተክርስትያን አገልግሎት ትወዳለህ። እኛ የሁለት ሰዓት የቤተክርስትያን አገልግሎት እንወዳለን። አንተ ፍጹም የሆነ የድምጽ ውጣ ውረድ ከረዜማ አለህ። ወንድሜም ፍጹም የሆነ የድምጽ ውጣ ውረድ ከረዜማ አለው። እሱ እንደኔ አይነስውር ነው።”

የሜሪ ቃላት በጥልቀት ነኩኝ፤ ታላቅ የሆነውን መንፈሷን በተጨማሪም የእናትና አባቷን መሰጠት ገልጧል።

የኋላኛው ቀን ቅዱሳን ከሌሎች የኢየሱስ ክርስቶስ ተከታዮች ጋር ሌሎችን ለመርዳት፣ ከፍ ለማድረግ እና ለመውደድ ሁልጊዜ መንገድ ይፈልጋሉ። እነሱ የጌታ ህዝብ ለመባል “አንዳችሁ የአንዳችሁን ሸክም … ለመሸከም፣ … ከሚያዝኑት ጋር ለማዘን … መጽናናትን ለሚፈልጉ ለማጽናናት” ፈቃደኞች ናቸው። 3

በእውነት ቀዳማዊውንና ሁለተኛውን ታላቅ ትዕዛዝ ለመኖር ይሻሉ። በሙሉ ልባችን እግዚአብሔር ን ስንወድ ለሌሎች ደህንነት ልባችንን በሚያምር የደግነት ዑደት እንዲመለስ ያደርጋል።

ከአመት አመት የኋላኛው ቀን ቅዱሳን በአለም ዙርያ የሚሰጡትን የአገልግሎት መጠን ማስላት የማይቻል ነው። ነገር ግን ቤተክርስትያኑ እንደ ድርጅት የእርዳታ እጅ የሚያስፈልጋቸው የአዋቂ ሴቶችንና ወንዶችን — ህጻናት ወንዶችና ሴቶች ላይ የሚሰራውን መልካም ተግባር ማስላት ይቻላል።

የቤተክርስትያኗ የሰብአዊ አገልግሎት የተጀመረው እ.ኤ.አ በ1984 ነው። ከዚያም በምስራቅ አፍሪካ በከፍተኛ ድርቅ ለተጎዱ ገንዘብ ለማሰባሰብ ቤተክርስትያን አቀፍ ጾም ተካሂዶ ነበር። በዚያች አንዲት የጾም ቀን የቤተክርስትያኗ አባላት 6.4 ሚሊዮን ዶላር ለገሱ።

ምስል
ከዛም ሽማግሌ ባላርድ በኢትዮጲያ

ከዚያም ሽማግሌ ኤም. ራስል ባላርድ እና ወንድም ግለን የተሰበሰበው ፈንድ እንዴት በተሻለ መንገድ መጠቀም እንዳለበት ለመገምገም ወደ ኢትዮጵያ ተልከው ነበር። ይህ ጥረት ኋላ ላይ የኋላኛው ቀን ቅዱሳን በጎ አድራጎት ለተባለው ጅማሬ እንደሆነ አረጋግጧል።

ከዚያን ጊዜ ጀምሮ የኋላኛው ቀን ቅዱሳን በጎ አድራጎት በአለም ዙሪያ እርዳታ ለሚያስፈልጋቸው ይረዳ ዘንድ ከሁለት ቢሊየንዶላር በላይ ለግሰዋል። ይህ እርዳታ የተሰጠው ከቤተክርስትያን ጋር ያላቸውን ዝምድና ፣ ዜግነት፣ ዘር፣ የጾታ ምርጫ፣ ጾታ ወይም የፖለቲክስ ምርጫን ከግምት ሳያስገባ ነው።

ይህ ብቻ አይደለም። በችግር ውስጥ ያሉ የጌታን ቤተክርስትያን አባላትን ለመርዳት ጥንታዊውን የጾም ህግ እንወዳለን እናም እንኖራለን። 4 የተራቡትን ለመርዳት እኛ እንራባለን። እርዳታ የሚያሻቸውን ለመርዳት በወር ውስጥ ለአንድ ቀን ምግብ አንመገብም እናም የዚያን ምግብ ዋጋ (እና ተጨማሪ ) እንለግሳለን።

ለመጀመርያ ጊዜ ወደ ምዕራብ አፍሪካ እ.ኤ.አ በ1986 ያደረኩትን ጉዞ በፍጹም አልረሳም። ቅዱሳን ወደ ስብሰባችን በብዙ ቁጥር መጡ። ምንም እንኳን አብዛኛዎቹ ያላቸው ንብረት ጥቂት ቢሆንም እንከን የሌለው ነጭ ልብስ ለብሰው ነበር።

የካስማ ፕሬዘደንቱን በጣም ጥቂት ያላቸውን አባላት እንዴት እንደሚንከባከብ ጠየኩት። እሱም ኤጶስ ቆጶሶቻቸው ህዝባቸውን በሚገባ ያውቁዋቸዋል ብሎ መለሰ። አባላቱ በቀን ሁለት ምግብ መመገብ የሚችሉ ከሆነ እርዳታ አያስፈልግም። ነገር ግን በቀን አንድ ምግብ ወይም ያነሰ የሚመገቡ ከሆነ—የቤተሰብም እርዳታ ተጨምሮ —ኤጵስ ቆጶሳቱ ምግብ፣ ገንዘብ ከጾም በኩራት ይሰጧቸዋል። ከዚያም ይህንን መጠቀስ የሚገባው እውነት አከለ፤ የጾም በኩራታቸው ብዙጊዜ ከወጪያቸው ይልቃል። የተረፈው የጾም በኩራት ሌላ ቦታ ለሚገኙ ከነሱ በላይ ለሚያስፈልጋቸው ሰዎች ይላካል። እነዚያ ቆራጥ አፍሪካውያን ቅዱሳን ስለጾም ህግ ሃይል እና የጾም መንፈስ ታላቅ ትምህርት አስተማሩኝ።

እንደ ቤተክርስትያን አባላት በማንኛውም አይነት ስቃይ ውስጥ ያሉትን እንረዳቸዋለን።5 እንደእግዚአብሄር ወንዶች እና ሴት ልጆች ሁላችንም ወንድሞችና እህቶች ነን። በብሉይ ኪዳን “በአገርህ ዉስጥ ላለው ድሃ ለተቸገረውም ወንድምህም እጅህን ትከፍታለህ ብዬ አዝዝሃለሁ።”6የሚለውን ተግሳጽ እንቀበላለን።

ማቴዎስ 25 ላይ ያለውን የጌታ የኢየሱስ ክርስቶስን አስተምሮ ለመኖርም እንጥራለን፤

“ተርቤ አብልታችሁልኛልና፤ ተጠምቼ አጠጥታችሁኛልና፤ እንግዳ ሆኜ ተቀብላችሁኛልና፤

“ታርዤ አልብሳችሁኛልና፤ ታምሜ ጠይቃችሁልኛልና። …

“…ከሁሉ ከሚያንሱ ከእነዚህ ወንድሞቼ ለአንዱ እንኳን ብታደርጉ ለኔ ነው ያደረጋችሁት” 7

እስቲ ቤተክርስትያኑ እንዴት የክርስቶስን አስተምሮት እንደሚከተል ጥቂት ምሳሌዎችን ልጥቀስ።

ምስል
ኤጶስ ቆጶሶች ግምጃ ቤት

ረሃብን ለማስታገስ እንዲረሳ በአለም ዙርያ ቤተክርስትያኑ 124 የኤጵስ ቆጶሳት ግምጃ ቤት ይሰራል። በነዚያ አማካኝነት በየአመቱ ወደ 400,000 የሚጠጉ የምግብ ትዕዛዞች እርዳታ ለሚያስፈልጋቸው ግለሰቦች ይሰጣሉ። ግምጃ ቤት በሌለባቸው አካባቢዎች ኤጵስ ቆጶሳት እና የቅርንጫፍ ፕሬዝደንቶች ከቤተክርስትያኑ የጾም በኩራት በመውሰድ ምግብ እና አቅርቦቶችን ለተቸገሩ አባላት ይሰጣሉ።

ሆኖም ግን የረሃብ ፈተና ከቤተክርስትያኗ ገደብ አልፎ ይሄዳል እናም በአለም ዙርያ እየጨመረ ነው። ስለ ዓለም አዳኝ ነው። የቅርብ ጊዜ የተባበሩት መንግስታት ዘገባ በአለም ላይ የምግብ እጥረት ያለባቸው ሰዎች ቁጥር አሁን ላይ ከ 820 ሚሊዮን በላይ — ወይም ከዚች ምድር ነዋሪዎች ከዘጠኙ አንዱ አካባቢ እንደሆነ ያመለክታል።8

እንዴት ያለ አሳስቢ የቁጥር መረጃ ነው! ስለመዋጮዋችሁ እንዴት አመስጋኞች ነን። ከልብ ስለሆነው ልግስናችሁ እናመሰግናለን፣ እጅግ ተፈላጊ ምግብ፣ ልብስ፣ ጊዚያዊ መጠለያ፣ ዊልቼር፣ መድሃኒቶች፣ንጹህ ውሃ እና ሌላም በአለም ዙርያ ሚሊዮኖች ይቀበላሉ።

በአለም ዙርያ ብዙ በሽታዎች የሚመጡት በንጹህ ዉሃ እጦት ነው። እስካሁን ባለው የቤተክርስትያኑ የእርዳታ ፕሮግራም በመቶዎች ለሚቆጠሩ በ 76 ሃገራት ለሚገኙ ማህበረሰቦች ንጹህ ውሃን በማቅረብ ረድቷል።

በኮንጎ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ሉፑታ ያለው ፕሮጀክት ትልቅ ምሳሌ ነው። ከ100,000 በላይ ህዝብ ለሚኖርባት ከተማ ምንም ውሃ የለም ። ዜጎች ንጹህ ዉሃ ለማግኘት ረጅም መንገድ መራመድ ይጠበቅባቸዋል። የተራራ ምንጭ ከ18 ማይል (29 ኪሎ ሜትር) ርቀት ቢገኝም የከተማው ህዝብ ግን በቋሚነት ያን ዉሃ ማግኘት አይችልም።

ምስል
ለውሀ ቦይ መቆፈ

እርዳታ አድራጊ ምስዮናውያኖቻችን ይህን ፈተና ሲረዱ ከሉፑታ መሪዎች ጋር እቃ በማቅረብ እና ዉሃዉን በቧንቧ ለከተማው እንዲደርስ በጋራ ሰርተዋል። የሉፑታ ህዝብ አንድ ሜትር ጥልቀት ያለው ቦይ በአለት እና በጫካ ውስጥ በመቆፈር ሶስት አመትፈጅተዋል። በአንድነት በመስራት በዚያች መንደር ለሚኖሩ ሁሉ ንጹህ ውሃ የሚገኝበት አስደሳቹ ቀን በመጨረሻ ደረሰ።

ምስል
ውሀ መሸከም

ቤተክርስትያኑ በእርስበርስ ግጭት ፣ በተፈጥሮ አደጋ ውድመት ፣ ወይም ሃይማኖታዊ ግጭት የተጎዱ ስደተኞችንም ይረዳል። ከ 70 ሚሊዮን በላይ ህዝብ በአሁን ሰዓት ከቤቶቻቸው ውጪ ናቸው።9

ምስል
ለስደተኛች ማስተማር

እ.ኤ.አ በ20018 ብቻ ቤተክርስትያኑ በ56 ሃገራት ለሚገኙ ስደተኞች ለድንገተኛ ጊዜ የሚሆን እቃ ለግሷል። በተጨማሪም ብዙ የቤተክርስትያን አባላት ስደተኞት ወደ አዲስ መንደር እንዲቀላቀሉ ለመርዳት ጊዝያቸውን ለግሰዋል። አዲስ ቤቶችን ለመመስረት እየሞከሩ የነበሩትን ለመርዳት የሞከራችሁት እያንዳንዳችሁን እናመሰግናለን።

ምስል
የልብስ ስርጭት

በየአመቱ በዩናይድ ስቴትስ ለዴዘረት ኢንደስትሪ በሚደረግ ልገሳ ሚሊዮን ፓውንድ የሚሆኑ ልብሶች ተሰብስበዋል እናም ተለይተዋል። በሃገር ውስጥ ያሉ ኤጵስ ቆጵዖሶች ይህንን አቅርቦት እርዳታ ለሚያስፈልጋቸው አባላት ቢጠቀሙም አብዛኛው ክፍል በአለም ዙርያ ለሚያሰራጩ ሌሎች በጎ አድራጊ ድርጅቶች ይለገሳል።

ባለፈው አመት፣ ቤተክርስትያኑ የእይታ ጥንቃቄ ከ 300,000 በላይ ሰዎች በ35 ሃገራት ፣ የአራስ ልጅ እንክብካቤ በሺዎች ለሚቆጠሩ እናቶች እና ጭቅላ ህጻናት በ 39 ሃገሮች፣ እና ዊንቼር በብዙ ሃገራት ከ 50,000 በላይ ለሆኑ ሰዎች አቅርቧል።

አደጋ ሲከሰት ቤተክርስትያኑ ቀድሞ ከሚደርሱት መሃል በመሆን ይታውቃል። አውሎ ነፋስ ከመከሰቱ በፊት የቤተክርስትያን መሪዎች እና በተጠቂ ቦታዎች ያሉ ሰራተኞች በጋራ በመሆን እንዴት የእርዳታ እቃ እና ለተጎዱት እንዴት በጎ አድራጎት ስራ እንደሚሰሩ እቅድ ያወጣሉ።

ምስል
በሚረዱ እጆች ማገልገል

ባለፈው አመት ብቻ ቤተክርስትያኑ ከ 100 በላይ የድንገተኛ ጊዜ እርዳታ ፕሮጀክት በአለም ዙርያ የአውለንፋስ፣ የእሳት፣ የጎርፍ፣ የመሬት መንቀጥቀጥ እና የሌሎች አደጋዎች ተጠቂዎችን ለመርዳት አቋቁሟል። በተቻለ አቅም የቤተክርስትያናችን አባላት ቢጫ የእርዳታ እጆች ልብስ በመልበስ ብዙ ቁጥር ያላቸውን በአደጋ የተጎዱትን ለመርዳት ይሞክራሉ። በብዙዎቻችሁ የሚሰጠው እንዲህ አይነት እርዳታ የአገልግሎት ፍሬ ነው።

ውድ ወንድሞች እና እህቶች የተናገርኳቸው በኋላኛው ቀን ቅዱሳን የኢየሱስ ክርስቶስ ቤተክርስትያን እያደገ ያለውን የበጎ አድራጎት እና የደህንነት እንቅስቃሴዎች ጥቂቶቹ ናቸው።10 እናም ይህ ሁሉ እንዲሆን ያደረጋችሁት እናንተ ናችሁ። ምሳሌ በሆነው ህይወታችሁ፣ ለጋስ ልብ እና የእርዳታ እጆቻችሁ ምክንያት ህብረተሰቡ እና የመንግስት መሪዎች ጥረታችሁን ማድነቃቸው አያስደንቅም። 11

የቤተክርስትያኑ ፕረዝደንት ከሆንኩ ጊዜ ጀምሮ ምን ያህል ብዙ ፕረዝደንቶች፣ ጠቅላይ ሚንስትሮች፣ እና አምባሳደሮች ለህዝባቸው ባደረግነው በጎ አድራጎት እርዳታ ከልባቸው እንዳመሰገኑኝ ተገርሚያለሁ። እናም ታማኝ አባሎቻችን ለሃገራቸው ታማኝ የሚጠቅሙ ዜጎች በመሆን ለሚያመጡት ጥንካሬ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

በተጨማሪም ቤተክርስትያኗ በሃገራቸው እንድትመሰረት ያላቸውን ተስፋ በገለጹ ቀዳሚ አመራሮችን በጎበኙ የአለም መሪዎችም ተደንቂያለሁ። ለምን? ምክርያቱም የኋላኛው ቀን ቅዱሳን ጠንካራ ቤተሰቦችን እና ማህበረሰብን ለመገንባት ስለሚረዱ እና በሚኖሩበት ቦታ ሁሉ ለሌሎች ህይወትን የተሻለ ስለሚያደርጉ ነው።

ቤታችን የትም ቢሆን የቤተክርስትያን አባላት ስለእግዚአብሔር አባትነት እና የሰው ልጅ ወንድማማችነት ከልባቸው ይሰማቸዋል። ስለዚህ በዚች አስደናቂ አለም ውስጥ የትም ብንኖር የእኛ ታላቁ ደስታ የሚመጣው ወንድሞቻችንን እና እህቶቻችንን ስንረዳ ነው።

የኛ ደስታ ለሌሎች እርዳታ በመስጠት ነው— በጥንቃቄ ለኛ እንደምናስበው ውይም ከዚያም በላይ ሌሎች መንከባከብ አለብን። በተለይም ሳይመቸን ሲቀር ወይም ከምቾት ቦታችን ሲያወጣን ብዬ እጨምራለሁ።መኖርእውነተኛ የኢየሱስ ክርስቶስ ደቀመዝሙር ለመሆን ሁለተኛይቱን ታላቅ ትዕዛዝ መኖር ቁልፍ ነው።

ውድ ወንድሞቼ እና እህቶቼ፣ የኢየሱስ ክርስቶስን አስተምሮት በመከተል የሚመጣ ፍሬ ህያው ምሳሌዎች ናችሁ። አመሰግናችኋለሁ! እወዳችኋለሁ!

እግዚአብሔር ህያው እንደሆነ አውቃለሁ። ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። በዚህ በመጨረሻው ቀን የሱን መለኮታዊ እቅድ ለማሟላት ቤተክርስትያኑ ዳግም ተመልሷል። ስለዚህ የምመሰክረው በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ነው፣ አሜን።