ምስክርነት ደግሞም መመስከር; መንፈስ ቅዱስ; ምስክር ተመልከቱ በመንፈስ ቅዱስ ብኩል የሚሰጥ እውቀት እና ምስክር። ምስክር ሰው እንደ እውነት ስለሚመለከተው በይፉ ወይም በህግ የሚያውጀው ሊሆንም ይችላል (ት. እና ቃ. ፻፪፥፳፮)። እኔን ግን የሚቤዠኝ ሕያው እንደ ሆነ አውቃለሁ, ኢዮብ ፲፱፥፳፭–፳፮. በጌታችን ምስክርነት አትፈር, ፪ ጢሞ. ፩፥፰. የኢየሱስ ምስክር የትንቢት መንፈስ ነው, ራዕ. ፲፱፥፲. በሁሉም ጊዜዎች እንደ እግዚአብሔር ምስክር ቁሙ, ሞዛያ ፲፰፥፱. በእነርሱ ላይ ንጹሁን ምስክር በግድ ከመገፋፋት በስተቀር እነርሱን መልሶ የሚያገኝበት ሌላ መንገድ የለም, አልማ ፬፥፲፱–፳. እነዚህ ነገሮች እውነት ለመሆናቸው ለምስክርነት ሁሉም ነገር አሉኝ, አልማ ፴፥፵፩–፵፬. እምነታችሁ እስከሚፈተን ድረስ ምስክርነትን አትቀበሉም, ኤተር ፲፪፥፮. ይህንን ነገር በተመለከተ በአምሮህ ሰላምን አልተናገርኩም? ከዚህ የተሻለ ከእግዚአብሔር ምን አይነት ምስክርነትን ታገኛለህ, ት. እና ቃ. ፮፥፳፪–፳፫. ስለእርሱ ከተሰጡት ብዙ ምስክሮች በኋላ፣ ይህም በመጨረሻ ስለእርሱ የምንሰጠው ምስክር ነው, ት. እና ቃ. ፸፮፥፳፪–፳፬. የላኳችሁ እንድትመሰክሩ እና ሰዎችን እንድታስጠነቅቁ ነው, ት. እና ቃ. ፹፰፥፹፩–፹፪. መስካሪዎቹ ሞተዋል፣ እና ምስክራቸውም ተፅዕኖ አለው, ት. እና ቃ. ፻፴፭፥፬–፭. ሔኖክ መላእክቶች የአብና ወልድ ምስክር ይዘው ከሰማይ ሲወርዱ አየ, ሙሴ ፯፥፳፯. ምንም እንኳን ራዕይ አይቻለሁ በማለቴ ብጠላና ብሰቃይም፣ ይህ ግን እውነት ነበር, ጆ.ስ.—ታ. ፩፥፳፬–፳፭.