ንጹህ፣ ንጹህነት ደግሞም ቅድስና; ንጹህ እና ርኩስ ተመልከቱ ከኃጢያት ወይም ጥፋት ነጻ መሆን፤ ታማኝ። ሰው ንጹህ የሚሆነው ሀሳቦቹ እና ስራዎቹ በሁሉም መንገድ የጸዱ ሲሆኑ ናቸው። ኃጢያት የሰራ ሰው በኢየሱስ ክርስቶስ እምነት፣ ንስሀ በመግባት፣ እና የወንጌልን ስነስርዓቶችን በመቀበል ንጹህ ለመሆን ይችላል። እጆቹ የነጹ፥ ልቡም ንጹሕ የሆነ የጌታን በረከት ይቀበላል, መዝ. ፳፬፥፫–፭. እናንተ የእግዚአብሔር ዕቃ የምትሸከሙ ሆይ፣ ንጹሐን ሁኑ, ኢሳ. ፶፪፥፲፩ (ት. እና ቃ. ፻፴፫፥፬–፭). ልበ ንጹሖች ብፁዓን ናቸው, ማቴ. ፭፥፰ (፫ ኔፊ ፲፪፥፰). ንጹሕ የሆነውን ነገር ሁሉ፥ እነዚህን አስቡ, ፊልጵ. ፬፥፰ (እ.አ. ፩፥፲፫). በልባችሁ ንፁህ የሆናችሁ ሁሉ፣ ራሳችሁን አቅኑ እናም አስደሳቹን የእግዚአብሔርን ቃል ተቀበሉ, ያዕቆ. ፫፥፪–፫. በዚያን ቀን በንፁህ ልባችሁና በንፁህ እጃችሁ እግዚአብሔርን ለመመልከት ትችላላችሁን, አልማ ፭፥፲፱. በአምላክ ፊት ንፁህና እንከን የለሽ ከሆኑ፣ ኃጢያትን ከመጥላት በቀር ሊመለከቱትም አልቻሉም, አልማ ፲፫፥፲፪. ክርስቶስ ንጹህ እንደሆነ ንጹህ ሁኑ, ሞሮኒ ፯፥፵፰ (ሞር. ፱፥፮). ክርስቶስ ንጹህ ህዝቦችን ለእራሱ ያቆያል, ት. እና ቃ. ፵፫፥፲፬. ጌታ ንጹህ የሆኑት እግዚአብሔርን የሚያዩበት ቤት በፅዮን እንዲገነባ አዘዘ, ት. እና ቃ. ፺፯፥፲–፲፯. ይህም ፅዮን ነውና—ልበ ንጹህ, ት. እና ቃ. ፺፯፥፳፩.