ትዕግስት ደግሞም መፅናት; ገር፣ ገርነት ተመልከቱ በጸጥተኛ መፅናናት፤ ስቃይን፣ ስድብን፣ ወይም ጉዳትን ያለማማረር ወይም ያለመበቀል የመፅናት ችሎታ። ለእግዚአብሔር ተገዛ ተስፋም አድርገው, መዝ. ፴፯፥፯–፰. ትዕግሥተኛ ሰው ብዙ ማስተዋል አለው, ምሳ. ፲፬፥፳፱. በመታገሣችሁም ነፍሳችሁን ታገኛላችሁ, ሉቃ. ፳፩፥፲፱. በመጽናትና በትእግስት ተስፋ ይሁንልን, ሮሜ ፲፭፥፬. በእምነትና በትዕግሥትም የተስፋውን ቃል የሚወርሱትን ተከታዮች ሁኑ, ዕብ. ፮፥፲፪–፲፭. ትዕግሥትም ፍጹማንና ምሉዓን ትሆኑ ዘንድ ሥራውን ይፈጽም, ያዕ. ፩፥፪–፬. ኢዮብ እንደ ታገሠ ሰምታችኋል, ያዕ. ፭፥፲፩. በደስታና በትዕግስት ለጌታ ፈቃድ ተቀባይ እንዲሆኑ ጌታ ብርታትን ሰጥቷቸዋል, ሞዛያ ፳፬፥፲፭. ጌታ ካንተ ጋር በመሆኑ እነዚህን ነገሮች ሁሉ በትዕግስት ጸንተሀል, አልማ ፴፰፥፬–፭. ፍጹም እስክትሆኑ ድረስ በትግስት ቀጥሉ, ት. እና ቃ. ፷፯፥፲፫.