መሀላ ደግሞም ቃል ኪዳን; የክህነት መሀላ እና ቃል ኪዳን ተመልከቱ በቅዱሣት መጻህፍት ውስጥ እንደሚጠቀሙበት፣ ቅዱስ ቃል ኪዳን ወይም የተስፋ ቃል። ነገር ግን፣ ከሰይጣን እና ከመላእክቶቹ በተጨማሪ፣ ኃጢያተኛ ሰዎች ክፉ አላማቸውን ለማከናወን መሀላዎችን ይገባሉ። በብሉይ ኪዳን ውስጥ፣ መሀላዎች ተቀባይ ነበሩ፤ ነገር ግን፣ ሰዎች በእግዚአብሔር ስም ወይም በእርሱ ፍጥረቶች መሀላ እንደማይገባቸው ኢየሱስ ክርስቶስ አስተማረ (ማቴ. ፭፥፴፫–፴፯)። ለአብርሃም የማልሁለትንም መሐላ አጸናለሁ, ዘፍጥ. ፳፮፥፫. ሰው ነፍሱን በመሐላ ቢያስር፥ ቃሉን አይስበር, ዘኁል. ፴፥፪. የእግዚአብሔርን ትእዛዝ ሁሉ ሥርዓቱን ይጠብቁና ያደርጉ ዘንድ መሐላውን አደረጉ, ነሀ. ፲፥፳፱. መሐላዎችህን ለጌታ ስጥ, ማቴ. ፭፥፴፫ (መክ. ፭፥፬–፭; ፫ ኔፊ ፲፪፥፴፫). እግዚአብሔር ታማኞች እንደሚድኑ መሀላ አደረገ, ዕብ. ፮፥፲፫–፲፰. ዞረም መሃላ ሲገባልን፣ ፍርሃቶች አቆሙ, ፩ ኔፊ ፬፥፴፯. የአሞን ህዝብ በጭራሽ ደም ላለማፍሰስ መሃላን ሰጥተው ነበር, አልማ ፶፫፥፲፩. ኃጢያተኞች ኔፋውያን የሚስጥር መሀላና ቃል ኪዳን ከሰይጣን ጋር ገቡ, ሔለ. ፮፥፳፩–፴. ሰዎች በክህነት ስልጣን መሀላና ቃል ኪዳን የዘለአለም ህይወት ያገኛሉ, ት. እና ቃ. ፹፬፥፴፫–፵፪. በመንፈስ ቅዱስ ቃል ኪዳን ያልታተሙ ቃል ኪዳናት፣ ስምምነቶች፣ የተፈረመበት መረጃዎች፣ ግዴታዎች፣ መሀላዎች፣ ሰዎች ሲሞቱ መጨረሻ አላቸው, ት. እና ቃ. ፻፴፪፥፯.