ክፉ መናገር ደግሞም ሐሰት; አሉባልታ; ወሬ; ጸብ ተመልከቱ ትክክል ያልሆኑ፣ የሚጎዱ፣ እና ክፉ የሆኑ ነገሮችን መናገር። በብዙ ጊዜ በቅዱሣት መጻህፍት ውስጥ እንደዚህ አይነት ንግግር የሚደረገው በሰው ላይ ጉዳት ለማምጣት ነው። አንደበትህን ከክፉ ከልክል, መዝ. ፴፬፥፲፫ (፩ ጴጥ. ፫፥፲). ምናምንቴ ሰው ክፋትን ይምሳል, ምሳ. ፲፮፥፳፯. ክፉውን ሁሉ በውሸት ሲናገሩባችሁ ብፁዓን ናችሁ, ማቴ. ፭፥፲፩ (፫ ኔፊ ፲፪፥፲፩). ከልብ ክፉ አሳብ ይወጣል, ማቴ. ፲፭፥፲፱ (ማር. ፯፥፳፩). በሕዝብህ አለቃ ላይ ክፉ ቃል አትናገር, የሐዋ. ፳፫፥፭. ክፋ ንግግሮች ሁሉ ከእናንተ ዘንድ ይወገድ, ኤፌ. ፬፥፴፩. እርስ በርሳችሁ አትተማሙ, ያዕ. ፬፥፲፩. መተማማት፣ ወይም ክፉ መነጋገር እንዳይኖር ይጠበቅ, ት. እና ቃ. ፳፥፶፬.