ክህደት ደግሞም አመጽ; የወንጌል ዳግም መመለስ ተመልከቱ በግለሰቦች፣ በቤተክርስትያን፣ ወይም በሕዝቦች ሁሉ ከእውነት ዞር ማለት። ታላቅ ክህደት እስራኤል ከጌታ ልቦቻቸው ከሚያስቱት ይጠብቁ, ዘዳግ. ፳፱፥፲፰. ራዕይ ባይኖር ሕዝብ መረን ይሆናል, ምሳ. ፳፱፥፲፰. የዘላለሙንም ቃል ኪዳን አፍርሰዋል, ኢሳ. ፳፬፥፭. ነፋስም ነፈሰ ያንም ቤት መታው፣ ወደቀም, ማቴ. ፯፥፳፯. ወደ ልዩ ወንጌል እንዲህ ፈጥናችሁ እንዴት እንዳለፋችሁ እደነቃለሁ, ገላ. ፩፥፮. በጥሩ መንገድ ጉዞ ጀመሩ፣ ነገር ግን መንገዳቸውን በጭጋግ ውስጥ ሳቱ, ፩ ኔፊ ፰፥፳፫ (፩ ኔፊ ፲፪፥፲፯). ፍሬውን ከቀመሱ በኋላ አፈሩ፤ ወደ ተከለከለውም መንገድ ገቡና ጠፉ, ፩ ኔፊ ፰፥፳፰. የኔፋውያን ክህደት ለማያምኑት መደናቀፊያ ሆነ, አልማ ፬፥፮–፲፪. የቤተክርስቲያኗ አባላት በኩራት ተወጠሩ እናም ሌሎች አባላትን አሳደዱ, ሔለ. ፫፥፴፫–፴፬ (ሔለ. ፬፥፲፩–፲፫; ፭፥፪–፫). ጌታ ህዝቡን ሲያበለፅግ፣ አንዳንዴ እነርሱ ልባቸውን ያጠጥራሉ እናም ይረሱታል, ሔለ. ፲፪፥፪፤ ፲፫፥፴፰. ኔፋውያን ልባቸውን አደነደኑ እናም በሰይጣን ሀይል ስርም ወደቁ, ፫ ኔፊ ፪፥፩–፫. ሞሮኒ ስለመጨረሻው ቀናት ክህደት ተነበየ, ሞር. ፰፥፳፰፣ ፴፩–፵፩. ከዳግም ምፅዓት በፊት ክህደት ይመጣል, ት. እና ቃ. ፩፥፲፫–፲፮. የመጀመሪያ የክርስትያን ቤተክርስትያን ክህደት ይህ ሕዝብ በአፉ ወደ እኔ ይቀርባል, ኢሳ. ፳፱፥፲፣ ፲፫. ጨለማ ምድርን ይሸፍናል, ኢሳ. ፷፥፪. ጌታ የእግዚአብሔርን ቃላትን የመስማት ራብን ይልካል, ዓሞ. ፰፥፲፩. ሐሰተኞች ክርስቶሶችና ሐሰተኞች ነቢያት ይነሣሉ, ማቴ. ፳፬፥፳፬. ጨካኞች ተኩላዎች በመካከላችሁ ይገባሉ, የሐዋ. ፳፥፳፱. ወደ ልዩ ወንጌል እንዲህ ፈጥናችሁ እንዴት እንዳለፋችሁ እደነቃለሁ, ገላ. ፩፥፮. ከዳግም ምፅአት በፊት ክህደት አስቀድሞ ይመጣል, ፪ ተሰ. ፪፥፫. አንዳንዶች ስለእውነት ይስታሉ, ፪ ጢሞ. ፪፥፲፰. አንዳንዶች የአምልኮት መልክ አላቸው ኃይሉን ግን ይክዳሉ, ፪ ጢሞ. ፫፥፪–፭. እውነት ትምህርትን የማይጸኑበት ጊዜ ይመጣል, ፪ ጢሞ. ፬፥፫–፬. ሐሰተኞች ነቢያት እና ሐሰተኞች በህዝቡ መካከል, ፪ ጴጥ. ፪፥፩. አንዳንዶች ሰዎች ሾልከው ብቻውን ያለውን ንጉሳችንን እና ጌታችንን ይክዳሉ, ይሁዳ ፩፥፬. አንዳንድ ሰዎች ሐዋርያት ነን ይላሉ እና አይደሉም, ራዕ. ፪፥፪. ኔፊ የታላቋና የርኩሰቱን ቤተክርስቲያን መመስረትን አየ, ፩ ኔፊ ፲፫፥፳፮. አህዛብ ተሰናክለዋል እና በዚህም ብዙ ቤተክርስቲያኖች ሰርተዋል, ፪ ኔፊ ፳፮፥፳. ከስርዓቴ እርቀዋል፣ እናም የዘላለማዊ ቃል ኪዳኔን አፍርሰዋልና, ት. እና ቃ. ፩፥፲፭. ጭለማ ምድርን፣ እና ታላቅ ጭለማም የህዝቦችን አዕምሮ ሸፍኗል, ት. እና ቃ. ፻፲፪፥፳፫. ጆሴፍ ሁሉም ቤተክርስቲያናት ስህተተኛ እስደሆኑ ተነገረው፤ ልባቸውም ከእግዚአብሔር የራቁ ነበሩ, ጆ.ስ.—ታ. ፩፥፲፱.