ክፍል ፵፮
በመጋቢት ፰፣ ፲፰፻፴፩ (እ.አ.አ.) በከርትላንድ ኦሀዮ ውስጥ በነቢዩ ጆሴፍ ስሚዝ በኩል ለቤተክስቲያኗ የተሰጠ ራዕይ። በዚህ በቤተክርስቲያኗ ቀደምት ጊዜያት፣ የቤተክርስቲያኗን ስርዓቶች ለማከናወን አንድ ወጥ የሆነ የአሰራር ሁኔታ አልነበረም። ነገር ግን፣ በቅዱስ ቁርባን ስብሰባዎች እና በሌሎች ጉባዔዎች የቤተክርስቲያኗን አባላትና በትጋት ቤተክርስቲያኗን እየመረመሩ ያሉትን የመቀበል ልምድ በመጠኑም ቢሆን ነበር። ይህ ራዕይ የስብሰባዎችን አካሄድና አመራር እና የመንፈስ ስጦታዎችን ስለመፈለግ እና ለይቶ ስለማወቅ ስላለው መመሪያ በተመለከተ የጌታን ፈቃድ ይገልጣል።
፩–፪፣ ሽማግሌዎች ሰብሰባዎችን መንፈስ ቅዱስ እንደመራቸው ማከናወን አለባቸው፤ ፫–፮፣ እውነትን የሚሹ ከቅዱስ ቁርባን ስብሰባዎች መገለል የለባቸውም፤ ፯–፲፪፣ እግዚአብሔርን ጠይቁ እናም የመንፈስ ስጦታዎችን ፈልጉ፣ ፲፫–፳፮፣ ከእነዚህም ስጦታዎች የጥቂቶቹ ዝርዝር፤ ፳፯–፴፫፣ የቤተክርቲያን መሪዎች የመንፈስን ስጦታዎች የመለየት ሀይል ተሰጥቷቸዋል።
፩ የቤተክርቲያኔ ህዝብ ሆይ፣ አድምጡ፤ እውነት እላችኋለሁ፣ እነዚህ ነገሮች ለእናንተው የሚነገሯችሁ ለእናንተ ሀጥቅም እና ትምህርት ነውና።
፪ ነገር ግን ምንም እንኳን እነዚህ ነገሮች ቢጻፉም፣ ከመጀመሪያው ጀምሮ እንዲሁም ፍጻሜ እስከሚሆንበት ወቅት፣ ሁሉንም ስብሰባዎች በመንፈስ ቅዱስ ምሪትና አመራር ሀእንዲያካሂዱ በሁሉም ጊዜያት ለቤተክርስቲያኔ ለሽማግሌዎች ተሰጥቷቸዋል።
፫ ሆኖም፣ በአለም ፊት ከሚደረጉት የህዝብ ስብሰባዎቻችሁ ውስጥ በፍጹም ማንንም ሀእንዳታስወጡ ታዛችኋል።
፬ እንዲሁም ማንንም ሀየቤተክርስቲያኗ አባል ከቅዱስ ቁርባን ስብሰባዎች እንዳታስወጡ ታዛችኋል፤ ሆኖም፣ ማንም በደልን ያደረገ ቢኖር እስኪያስተሰርይ ድረስ ቅዱስ ቁርባንን ለእንዲወስድ አትፍቀዱለት።
፭ ደግሞም እንዲህ እላችኋለሁ፣ ማናቸውንም መንግስትን በትጋት እየፈለጉ ያሉትን ከቅዱስ ቁርባን ስብሰባዎቻችሁ አታስወጧቸው—ይህንን የምናገረውም በቤተክርቲያኗ አባል ስላልሆኑት ነው።
፮ ደግሞም እንዲህ እላችኋለሁ፣ ሀበማረጋገጫ ስብሰባዎቻችሁ ውስጥ የቤተክርቲያን አባል ያልሆኑ፣ በፅኑ መንግስትን የሚሹ፣ የሚገኙ ቢሆን አታስወጧቸው።
፯ ነገር ግን በልግስና የሚሰጠውን እግዚአብሔርን ስለሁሉም ነገሮች ሀእንድትጠይቁት ታዛችኋል፤ እናም መንፈስ የሚመሰክርላችሁንም ሁሉ በልብ ለቅድስና፣ በፊቴ በቅንነት በመራመድ፣ የደህንነታችሁን ፍጻሜ ሐእያሰባችሁ፣ ሁሉንም ነገሮች በጸሎትና መበምስጋና በማድረግ፣ በክፉመናፍስት ወይም ሠበአጋንንት ትምህርት ወይም በሰዎች ረትእዛዛት ሰእንዳትወሰዱ የእኔ ፈቃድ ነው፤ አንዳንዶቹ ከሰዎች ሌሎቹ ደግሞ ከአጋንንት ናቸውና።
፰ ስለዚህ፣ እንዳትታለሉ ተጠንቀቁ፤ እና ዘወትር ለምን እንደተሰጧችሁ እያስታወሳችሁ፣ እንዳትታለሉም የሚበልጠውን የጸጋ ስጦታ በፅኑ ሀፈልጉ፤
፱ በእውነት እላችኋለሁ፣ እነዚህ ለሚወዱኝ እና ሁሉንም ትእዛዛቴን ለሚጠብቁ እናም ይህን ለማድረግ ፈቃድ ላላቸው ለእነርሱ ጥቅም የተሰጡ ናቸው፤ ለምኞቶቻችሁ ሀማስፈፀሚያ በክፉ ለለምልክት ሳይጠይቁ፣ ከእኔ የሚሹት ወይም ይጠየቁበት ዘንድ እንዲጠቀሙበት ነው።
፲ እና ደግሞም በእውነት እላችኋለሁ፣ እነዚህ ለቤተክርቲያኗ የተሰጡት ሀስጦታዎች ምን እንደሆኑ፣ ሁል ጊዜም እንድታስታውሷቸውና ለበአዕምሮአችሁ እንድትጠብቋቸው ፍቃዴ ነው።
፲፩ ብዙ ስጦታዎች አሉ፣ ሁሉም ስጦታዎች ለሁሉም አልተሰጡም፤ ሀእያንዳንዱም ሰው አንድ ስጦታ በእግዚአብሔር መንፈስ ተስጥቶታል።
፲፪ ሁሉም በዚህም እንዲጠቀሙበት፣ ለአንዳንዶቹ አንድ ተሰጥቷል፣ እና ለሌሎችም ሌላ ተሰጥቷል።
፲፫ ለአንዳንዶቹ ኢየሱስ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደሆነ፣ እና ለአለምም ኃጢአት እንደተሰቀለ ሀእንዲያውቁ በመንፈስ ቅዱስ ተሰጥቷቸዋል።
፲፬ በታማኝነትም ቢቀጠሉ ዘለአለማዊ ህይወት እንዲኖራቸው፣ ለሌሎችም በእነርሱ ቃላት ሀእንዲያምኑ ተሰጥቷቸዋል።
፲፭ እናም ደግሞም፣ ለአንዳንዶቹ፣ አንዱን ጌታ እንደሚያስደስተው፣ እንደ ጌታ ፈቃድ፣ እንደ ሰው ልጆች ሁኔታዎች ምህረቱን በማመቻቸት፣ በመንፈስ ቅዱስ የአስተዳደርን ሀልዩነት እንዲያውቁ ተስጥቷቸዋል።
፲፮ ደግሞም፣ ለሌሎችም ስለ አሰራር ልዩነት፣ ከእግዚአብሔርም እንደሚመጡ፣ መንፈስን መግለጥ ለእያንዳንዱ ለጥቅም እንደሚሰጠው፣ እንዲያውቁ በመንፈስ ቅዱስ ይሰጣቸዋል።
፲፯ እናም ዳግም፣ እውነት እላችኋለሁ፣ ለአንዳዶቹ በእግዚአብሔር መንፈስ፣ ሀየጥበብ ቃል ተስጥቷቸዋል።
፲፰ ለሌላም፣ ሁሉም ብልህ እንዲሆኑ እና ሀእውቀት እንዲኖራቸው ይማሩ ዘንድ፣ የእውቀት ቃል ተስጥቷቸዋል።
፲፱ ደግሞም፣ ለአንዳንዶቹ ለመፈወስ ሀእምነት እንዲኖራቸው ተሰጥቷቸዋል፤
፳ እናም ለሌሎች ሀይፈውሱ ዘንድ እምነት እንዲኖራቸው ተስጥቷቸዋል።
፳፩ ደግሞም፣ ለአንዳንዶቹ ሀተዓምራትን ማድረግ ተሰጥቷቸዋል።
፳፪ እና ለሌሎችም ሀትንቢትን መናገር ተሰጥቷቸዋል።
፳፫ እና ለሌሎችም መናፍስትን ሀለመለየት ተሰጥቷቸዋል።
፳፬ ደግሞም፣ ለአንዳንዶች ሀበልሳን መናገር ተሰጥቷቸዋል።
፳፭ እና ለሌላውም በልሳኖች የተነገረውን መተርጎም ተሰጥቶታል።
፳፮ እናም እነዚህ ሀስጦታዎች ሁሉ፣ ለእግዚአብሔር ለልጆች ጥቅም፣ ከእግዚአብሔር የመጡ ናቸው።
፳፯ ለቤተክርቲያኗ ሀኤጲስ ቆጶስ፣ እናም ቤተክርቲያኗን እንዲጠብቁና የቤተክርቲያኗ ሽማግሌዎች እንዲሆኑ በእግዚአብሔር ለተመደቡት እና ለተሾሙትም፣ ከመካከላችሁ ከእግዚአብሔር የመጣ ያልሆኑትን ነገሮች ናቸው እንዳይሉ እነዚህን ስጦታዎች ለለይተው እንዲያውቁ ተሰጥቷቸዋል።
፳፰ እናም እንዲህ ይሆናል፣ ሀበመንፈስ የሚጠይቅ እርሱ በመንፈስም ይቀበላል፤
፳፱ ለአንዳንዶቹ እነዚህ ሁሉ ስጦታዎች የሚሰጧቸውም፣ መሪም እንዲኖር፣ እያንዳንዱ አባላት በዚህ ይጠቀሙበት ዘንድ ነው።
፴ ሀበመንፈስ ለየሚጠይቀው እርሱ እንደ እግዚአብሔር ሐፈቃድ ይጠይቃል፤ ስለዚህ እንደጠየቀውም ተደርጓለታል።
፴፩ ደግሞም፣ እንዲህ እላችኋለሁ፣ በመንፈስ ምንም ስታደርጉ፣ ሁሉም ነገሮች በክርስቶስ ስም መደረግ አለባቸው፤
፴፪ እናም ለማንኛውም የተባረካችሁባቸው በረከቶች ሀምስጋናን በመንፈስ ለእግዚአብሔር መስጠት አለባችሁ።
፴፫ እና በፊቴም ሀመልካምነትንና ለቅድስናን ሁል ጊዜ መለማመድ አለባችሁ። እንዲህም ይሁን። አሜን።