ክፍል ፲፰
ሰኔ ፲፰፻፳፱ (እ.አ.አ.) በፈየት፣ ኒው ዮርክ፣ ለነቢዩ ጆሴፍ ስሚዝ፣ ኦሊቨር ካውድሪ፣ እና ዴቪድ ዊትመር የተሰጠ ራዕይ። ነቢዩ እንዳለው፣ ይህ ራዕይ እንዲታወቅ የተደረገው “ስለአስራ ሁለት ሐዋሪያት በእነዚህ በኋለኛው ቀናት መጠራት ነበር፣ እና ደግሞም ቤተክርስቲያኗን ለመገንባት መመሪያዎችን ስለመስጠት ነበር።”
፩–፭፣ ቅዱሳን መጻህፍት ቤተክርስቲያን እንዴት እንደሚገነባ ያሳያሉ፤ ፮–፰፣ አለም በኃጢአት እየበሰለ ነው፤ ፱–፲፮፣ የነፍሳት ዋጋ ታላቅ ነው፤ ፲፯–፳፭፣ ደህንነትን ለማግኘት ሰዎች የክርስቶስን ስም በላያቸው ላይ መውሰድ አለባቸው፤ ፳፮–፴፮፣ የአስራ ሁለቱ ጥሪ እና ተልዕኮ ተገልጧል፤ ፴፯–፴፱፣ ኦሊቨር ካውድሪ እና ዴቪድ ዊትመር አስራ ሁለቱን መፈለግ ይገባቸዋል፤ ፵–፵፯፣ ደህንነትን ለማግኘት ሰዎች ንሰሀ መግባት፣ መጠመቅ፣ እና ትእዛዛቶቹን መጠበቅ አለባቸው።
፩ አሁን፣ እነሆ፣ አንተ አገልጋዬ፣ ኦሊቨር ካውድሪ ከእኔ ለማወቅ በምትሻው ነገር ምክንያት፣ እነዚህን ቃላት ለአንተ እሰጥሀለሁ፥
፪ እነሆ፣ አንተ የጻፍካቸው ነገሮች ሀእውነት እንደሆኑ፣ በብዙ አጋጣሚ በመንፈሴ ገልጬልሀለሁ፤ ስለዚህም እውነት እንደሆኑ ታውቃለህ።
፫ እናም እውነት እንደሆኑ ካወቅህ፣ እነሆ፣ ሀበተጻፉት ላይ እንድትደገፍ፣ ትእዛዛትን ለአንተ እሰጥሀለሁ፤
፬ ስለሆነ በውስጣቸው የቤተክርስቲያኔን፣ ሀየወንጌሌን፣ እና ለየአለቴን መሰረት በተመለከተ ሁሉም ነገሮች ተጽፈዋል።
፭ ስለዚህ፣ በወንጌሌ እና በአለቴ መሰረት ላይ ቤተክርስቲያኔን ከገንባህ የሲዖል ደጆችም አይቋቋሙህም።
፮ እነሆ፣ ሀአለም በኃጢአት እየበሰለ ነው፣ እናም የሰው ልጆች፣ ለአሕዛብ እና ደግሞም የእስራኤል ቤት፣ ለንስሀ መነሳሳት አለባቸው።
፯ ስለዚህ፣ እኔ ባዘዝኩት መሰረት በአገልጋዬ በጆሴፍ ስሚዝ፣ ዳግማዊ፣ እጅ ሀእንደተጠመቅህ ሁሉ፣ ያዘዝኩትን ነገር ፈጽሟል።
፰ በእኔ ለሚታወቀው አላማ፣ ለአላማዬ ስለጠራሁት አትደነቅ፤ ስለዚህ፣ ትእዛዛቴን ሀበመጠበቅ ለትጉህ ከሆነ፣ በዘለአለም ህይወት ሐይባረካል፤ ስሙም መጆሴፍ ነው።
፱ እናም አሁን፣ በትእዛዝ መልክ ለአንተ ለኦሊቨር ካውድሪ እናም እንዲሁም ለዴቭድ ዊትመር እናገራለሁ፤ ስለሆነም፣ እነሆ፣ በሁሉም ስፍራ ሁሉም ሰዎች ንስሀ እንዲገቡ አዝዛለሁና፣ እናም እርሱ በተጠራበት ጥሪ ስለተጠራችሁ እንደ ሀኃዋሪያዬ ጳውሎስ እናገራችኋለሁ።
፲ ሀየነፍስ ለዋጋ በእግዚአብሔር ፊት ታላቅ እንደሆነ አስታውሱ፤
፲፩ ስለሆነም፣ እነሆ ጌታ ሀአዳኛችሁ የስጋ ለሞትን ሞተ፤ ስለዚህ ሰዎች ንስሀ ገብተው ወደ እርሱ ይመጡ ዘንድ የሰዎችን ሁሉ ሐህመም መተሰቃየ።
፲፪ እናም ሀበንስሀ ብቻ ሰዎችን ሁሉ ወደእርሱ ያመጣ ዘንድ፣ ከሞት ዳግም ለተነሳ።
፲፫ እናም ንስሀ በሚገባ ነፍስ ሀደስታው እንዴት ታላቅ ነው!
፲፬ ሰለዚህ፣ ለዚህ ህዝብ ንስሀን ሀእንድትጮሁ ተጠርታችኋል።
፲፭ እናም በቀኖቻችሁ ሁሉ ንስሀን ወደ እነዚህ ህዝብ በመጮህ ብታገለግሉ፣ እናም አንድም ነፍስ ቢሆን እንኳን ወደ እኔ ዘንድ ብታመጡ፣ በአባቴ መንግስት ከእርሱ ጋር ሀደስታችሁ እንዴት ታላቅ ይሆናል!
፲፮ እናም አሁን፣ ወደ አባቴ ሀመንግስት ባመጣችሁት አንድ ነፍስ ደስታችሁ ታላቅ ከሆነ፣ ወደ እኔ ብዙ ነፍሳትን ለብታመጡ ሐደስታችሁ ምን ያህል ታላቅ ይሆናል!
፲፯ እነሆ፣ ወንጌሌ፣ እና አለቴ፣ እናም ሀማዳኔም በፊታችሁ ነው።
፲፰ እንደምትቀበሉ በማመን በእምነት አባቴን ሀበስሜ ለጠይቁ፣ እናም ለሰው ልጆች ሐአስፈላጊ የሆኑትን ነገሮች ሁሉ የሚገልጠው መንፈስ ቅዱስ ይኖራችኋል።
፲፱ እናም ሀእምነት፣ ለተስፋ፣ እናም ሐለጋስነት ከሌላችሁ፣ ምንም ነገር ማድረግ አትችሉም።
፳ ሀየዲያብሎስ ቤተክርስቲያን ካልሆነ በስተቀር ከማንም ቤተክርስቲያን ጋር ለአትከራከሩ።
፳፩ የክርስቶስ ሀስም በላያችሁ ላይ ውሰዱ እናም እውነትን ለበቅንነት ሐተናገሩ።
፳፪ እናም ስሜ በሆነው በኢየሱስ ክርስቶስ ሁሉ ንስሀ የሚገቡና ሀየሚጠመቁ እናም እስከመጨረሻው ድረስ ለየሚጸኑ፣ እንዲሁ ይድናሉ።
፳፫ እነሆ፣ ኢየሱስ ክርስቶስ ከአብ ዘንድ የተሰጠ ሀስም ነው፣ እናም ሰው ሊድንበት የሚችል የተሰጠ ሌላ ስም የለምና፤
፳፬ ስለዚህ ይህን፣ ከአብ የተሰጠውን ስም ሁሉም ሰዎች በራሳቸው ላይ ሊወስዱ ይገባል፣ በመጨረሻውም ቀን በዚያ ስም ይጠራሉና፤
፳፭ ስለዚህ፣ የሚጠሩበትን ሀስም የማያውቁ ከሆነ፣ በአባቴ ለመንግስት ስፍራ ሊኖራቸው አይችልም።
፳፮ እናም አሁን፣ እነሆ፣ ለአይሁድ እና ሀለአህዛብ ወንጌሌን እንዲያውጁ የተጠሩ ሌሎች አሉ።
፳፯ አዎን፣ እንዲሁም አስራ ሁለቱ፤ እናም ሀአስራ ሁለቱ ደቀመዛሙርቴ ይሆናሉ፣ እናም በላያቸው ላይ ለስሜን ይወስዳሉ፤ እናም አስራ ሁለቱም ዓላማ በተሞላ ልብ ስሜን በላያቸው ለመውሰድ ፈቃድ ያላቸው ናቸው።
፳፰ እናም አላማ በተሞላ ልብ ስሜን በላያቸው ላይ ሊወስዱ ፈቃድ ካላቸው፣ ወደ ሀአለም ሁሉ በመሄድ ለወንጌሌን ሐለፍጥረታት ሁሉ ለማወጅ ተጠርተዋል።
፳፱ እናም በተጻፈው መሰረት በስሜ ሀለማጥመቅ የተሾሙት እነርሱ ናቸው፤
፴ እናም የተጻፈው በፊታችሁ አለላችሁ፤ ስለዚህ፣ በተጻፉት ቃላት መሰረት ልታከናውኑት ይገባል።
፴፩ እናም ለእናንተ ሀለአስራ ሁለቱ እናገራለሁ—እነሆ፣ ጸጋዬ ለእናንተ በቂ ነው፤ በፊቴ በቅንነት ተራመዱ እናም ኃጢአትንም አታድርጉ።
፴፪ እናም፣ እነሆ፣ በመንፈስ ቅዱስ ኃይል፣ እናም እግዚአብሔር ለሰዎች በሰጠው ሀጥሪ እና ስጦታ ለመሰረት ካህናትን እና መምህራንን ሐእንድትሾሙ፣ እና ወንጌሌንም እንድታውጁ ዘንድ፣ በእኔ የተሾማችሁት እናንት ናችሁ፤
፴፫ እናም እኔ፣ ጌታችሁ እና አምላካችሁ ኢየሱስ ክርስቶስ ይህን ተናግሬዋለሁ።
፴፬ እነዚህ ሀቃላት የእኔ እንጂ የሰው ወይም የሰዎች አይደሉም፤ ስለዚህ፣ የሰው እንዳልሆኑ እናም የእኔ እንደሆኑ ትመሰክራላችሁ፤
፴፭ ለእናንተ እነዚህን የሚናገራችሁ ሀድምፄ ነው፤ ለእናንተም የተሰጧችሁ በመንፈሴ ነው፣ እናም በኃይሌም አንዳችሁ ለሌላኛችሁ ልታነቧቸው ትችላላችሁ፤ እናም በሀይሌ ካልሆነ በስተቀር እነርሱ ሊኖሯችሁ ባትችሉም ነበር፤
፴፮ ስለዚህ፣ ድምፄን እንደሰማችሁ እና ቃላቴን እንደምታውቁ ሀመመስከር ትችላላችሁ።
፴፯ እናም አሁን፣ እነሆ፣ ለአንተ ለኦሊቨር ካውድሪ እና እንዲሁም ለዴቪድ ዊትመር የተናገርኩት ነገር ፈቃድ ያላቸውን አስራ ሁለቱን ኃዋሪያት እንድትፈልጉ ኃላፊነትን ሰጥቻችኋለሁ፤
፴፰ እናም በፍላጎታቸው እና ሀበስራቸው ታውቋቸዋላችሁ።
፴፱ እናም ባገኛችኋቸው ጊዜ እነዚህ ነገሮች ታሳይዋቸዋላችሁ።
፵ እናም ትሰግዳላችሁ እናም አባቴን በስሜ ሀታመልካላችሁ።
፵፩ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ንስሀ ሊገቡ እንደሚገባ እና መጠመቅም እንዳለባቸው በማለት ለአለም መስበክ ይኖርባችኋል፤
፵፪ ሁሉም ወንዶች ንሰሀ መገባት እና መጠመቅ አለባቸው እናም ወንዶች ብቻ ሳይሆኑ ነገር ግን ሴቶች፣ እናም ሀለተጠያቂነት እድሜ የደረሱ ልጆች ሁሉ ንሰሀ መግባት እና መጠመቅ አለባቸው።
፵፫ እናም፣ አሁን፣ ይህንን ከተቀበላችሁ በኋላ፣ በሁሉም ነገሮች ሀትእዛዛቴን መጠበቅ አለባችሁ።
፵፬ እናም፣ ወደ ንስሀ እንዲመጡ ብዙ ኃጢዓቶቻቸውንም ሀበማሳመን፣ ወደ አባቴ መንግስት ይመጡ ዘንድ፣ በእጃችሁ ለድንቅ ስራን በሰዎች ልጆች መካከል እሰራለሁ።
፵፭ ስለዚህ፣ የምሰጣችሁ በረከቶች ከሁሉም ነገሮች ሀበላይ ናቸው።
፵፮ እናም ይህን ነገር ከተቀበላችሁ በኋላ፣ ትእዛዛቴን ሀየማትጠብቁ ከሆነ በአባቴ መንግስት አትድኑም።
፵፯ እነሆ፣ እኔ፣ ጌታችሁ እና አምላካችሁ እና አዳኛችሁ ኢየሱስ ክርስቶስ በመንፈሴ ሀይል ይህን ተናግሬዋለሁ። አሜን።